-
ምሕረት በማሳየት ረገድ ይሖዋን ምሰሉትመጠበቂያ ግንብ—1998 | ጥቅምት 1
-
-
17. (ሀ) በመጀመሪያው መቶ ዘመን በቆሮንቶስ ውስጥ ምን ሁኔታ ተከስቶ ነበር? ጳውሎስስ የጉባኤው አባሎች ጉዳዩን እንዴት እንዲመለከቱት መከራቸው? (ለ) የጳውሎስ ማሳሰቢያ ተግባራዊ የነበረው ለምን ነበር? በዛሬው ጊዜ እኛስ እንዴት ተግባራዊ ልናደርገው እንችላለን? (በተጨማሪም በስተቀኝ የሚገኘውን ሣጥን ተመልከት።)
17 በዚህ ረገድ ራሳችንን ለመመርመር እንዲረዳን በ55 እዘአ ገደማ በቆሮንቶስ ውስጥ የተከሰተውን ተመልከቱ። በዚያ ከጉባኤው ተወግዶ የነበረ አንድ ሰው ሕይወቱን አስተካክሎ መምራት ጀመረ። ወንድሞች ምን ማድረግ ነበረባቸው? ንስሐ መግባቱን በጥርጣሬ በመመልከት ከእሱ መራቃቸውን መቀጠል ነበረባቸውን? ከዚህ በተቃራኒ ጳውሎስ የቆሮንቶስ ሰዎችን እንዲህ ሲል አሳስቧቸዋል:- “እንደዚህ ያለው ከልክ በሚበዛ ኀዘን እንዳይዋጥ፣ ይልቅ ተመልሳችሁ ይቅር ማለትና ማጽናናት ይገባችኋል። ስለዚህ ከእርሱ ጋር ፍቅርን እንድታጸኑ እለምናችኋለሁ።” (2 ቆሮንቶስ 2:7, 8) አብዛኛውን ጊዜ ክፉ ሠርተው ንስሐ የገቡ ሰዎች በተለይ የኃፍረትና የተስፋ መቁረጥ ስሜት እንደሚሰማቸው የታወቀ ነው። በመሆኑም እነዚህ ሰዎች መሰል አማኞችና ይሖዋ እንደሚወዷቸው የሚያሳይ ማረጋገጫ ማግኘት ይፈልጋሉ። (ኤርምያስ 31:3፤ ሮሜ 1:12) ይህ በጣም አስፈላጊ ነው። ለምን?
-
-
ምሕረት በማሳየት ረገድ ይሖዋን ምሰሉትመጠበቂያ ግንብ—1998 | ጥቅምት 1
-
-
19 አሁን ደግሞ ንስሐ የገባውን ሰው ይቅር ለማለት ፈቃደኛ ባለመሆን ወደ ሌላኛው ጽንፍ ከሄዱ ሰይጣን በሌላ አቅጣጫ ሊያስታቸው ነው ማለት ነው። እንዴት? ሰይጣን የእነሱን ጨካኝና ምሕረት የለሽ መሆን እንደ መሣሪያ አድርጎ ሊጠቀም ይችላል። ንስሐ የገባው ኃጢአተኛ “ከልክ በሚበዛ ኀዘን ከተዋጠ” ወይም ቱደይስ ኢንግሊሽ ቨርሽን እንደሚለው “ሙሉ በሙሉ እጁን እስኪሰጥ ድረስ ካዘነ” ሽማግሌዎች በይሖዋ ፊት በኃላፊነት ይጠየቃሉ! (ከሕዝቅኤል 34:6 እና ከያዕቆብ 3:1 ጋር አወዳድር።) ኢየሱስ ተከታዮቹ “ከእነዚህ ከታናናሾች አንዱን” ከማሰናከል እንዲቆጠቡ ካስጠነቀቀ በኋላ እንዲህ ብሏል:- “ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ወንድምህ ቢበድልህ ገሥጸው፣ ቢጸጸትም ይቅር በለው።”a—ሉቃስ 17:1–4፣ በሰያፍ የጻፍነው እኛ ነን።
-