-
ጽናት ለክርስቲያኖች እጅግ አስፈላጊ ነውመጠበቂያ ግንብ—1993 | መስከረም 15
-
-
17. (ሀ) ኢየሱስ በጽናት የተቋቋመው ምን ዓይነት መከራዎችን ነው? (ለ) ኢየሱስ በጽናት የቻለው መከራ ምን ያህል ከባድ እንደነበረ ከምን መረዳት ይቻላል? (የግርጌ ማስታወሻውን ተመልከት።)
17 መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስን ‘ትኩር ብለን እንድንመለከትና’ ስለ እርሱም ‘እንድናስብ’ አጥብቆ ይመክረናል። ኢየሱስ የጸናባቸው መከራዎች ምንድን ናቸው? ከፈተናዎቹ አንዳንዶቹ በሌሎች ኃጢአትና አለፍጽምና ምክንያት የመጡ ናቸው። ኢየሱስ ችሎ የጸናው ‘ከኀጢአተኞች የደረሰበትን መቃወም’ ብቻ ሳይሆን በደቀ መዛሙርቱ መካከል ማን ታላቅ እንደሚሆን የተነሳውን ተደጋጋሚ ጭቅጭቅና በመካከላቸው የተነሱ ሌሎች ችግሮችን ጭምር ነበር። ከዚህም በላይ በማንም ላይ ደርሶ የማያውቅ የእምነት ፈተናም አጋጥሞታል። ‘በመከራ እንጨት ላይ እስከመሞት ጸንቷል።’ (ዕብራውያን 12:1–3 አዓት፤ ሉቃስ 9:46፤ 22:24) መሰቀሉና የአምላክን ስም እንደተሳደበ ተቆጥሮ በውርደት መገደሉ ያስከተለበትን የአእምሮና የአካል ሥቃይ መገመት እንኳን ያስቸግራል።a
18. ሐዋርያው ጳውሎስ በተናገረው መሠረት ኢየሱስን የረዱት ምን ሁለት ነገሮች ናቸው?
18 ኢየሱስን እስከ መጨረሻው እንዲጸና ያስቻለው ነገር ምንድን ነው? ሐዋርያው ጳውሎስ ኢየሱስን የረዱትን ሁለት ነገሮች ጠቅሷል። እነርሱም:- ‘ጸሎትና ምልጃ’ እንዲሁም ‘በፊቱ ያለው ደስታ’ ናቸው። ፍጹሙ የአምላክ ልጅ ኢየሱስ እርዳታ ለመጠየቅ አላፈረም። “በብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር” ወደ አምላክ ጸለየ። (ዕብራውያን 5:7፤ 12:2) በተለይ የመጨረሻው ከፍተኛ መከራ የሚደርስበት ጊዜ እየተቃረበ ሲሄድ ጥንካሬ እንዲሰጠው በተደጋጋሚና በጥብቅ መጸለይ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል። (ሉቃስ 22:39–44) ይሖዋ ኢየሱስ ላቀረበው ምልጃ መልስ የሰጠው መከራውን በማስወገድ ሳይሆን መከራውን ለመቋቋም የሚያስችለውን ብርታት በመስጠት ነበር። ኢየሱስ የጸናው ከመከራው እንጨት በስተጀርባ የሚያገኘውን ሽልማት ማለትም ለይሖዋ ስም መቀደስና የሰውን ልጆች ቤተሰብ ከሞት ለመቤዠት አስተዋጽዖ በማድረጉ የሚያገኘውን ደስታ አሻግሮ ስለተመለከተ ነው። — ማቴዎስ 6:9፤ 20:28
-
-
ጽናት ለክርስቲያኖች እጅግ አስፈላጊ ነውመጠበቂያ ግንብ—1993 | መስከረም 15
-
-
20 አንዳንድ ጊዜ እያነባን ለመጽናት እንገደድ ይሆናል። ኢየሱስን ያስደሰተው በመከራ እንጨት ላይ የደረሰበት ሥቃይ አልነበረም። ከዚህ ይልቅ እርሱን ያስደሰተው በፊቱ ያለው ሽልማት ነበር። እኛም ፈተና ሲደርስብን ሁልጊዜ በደስታ እንፈነድቃለን ብለን ካሰብን የማይቻለውን ነገር መጠበቅ ይሆንብናል። (ከዕብራውያን 12:11 ጋር አወዳድር።) ይሁን እንጂ ሽልማታችንን አሻግረን በመመልከት የሚያጋጥመንን በጣም አስቸጋሪ የሆነ ሁኔታ እንኳን ‘እንደ ሙሉ ደስታ’ ልንቆጥር እንችላለን። (ያዕቆብ 1:2–4፤ ሥራ 5:41) ዋናው ነገር እያነባንም ቢሆን ጸንተን መቆየታችን ነው። ኢየሱስ ያለው ‘ከሁሉ ያነሰ እንባ ያፈሰሰ ይድናል’ ሳይሆን “እስከ መጨረሻው የሚጸና . . . እርሱ ይድናል” ነው። — ማቴዎስ 24:13
-