-
“ለእምነት በብርቱ ተጋደሉ”!መጠበቂያ ግንብ—1998 | ሰኔ 1
-
-
5. ይሁዳ ጠቅሶ የጻፈው ከየትኛው የጥንት ነቢይ ነው? ትንቢቱስ ያለ ምንም ጥርጥር የሚፈጸም መሆኑን የሚያመለክተው እንዴት ነው?
5 ቀጥሎም ይሁዳ ከዚህ የበለጠ ታላቅ ፍርድ እንደሚኖር አመልክቷል። በመንፈስ አነሳሽነት በተጻፉት ቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ በሌላ በየትኛውም ቦታ ላይ የማይገኘውን የሄኖክን ትንቢት ጠቅሷል።a (ይሁዳ 14, 15) ሄኖክ አምላካዊ ባሕርይ የሌላቸው ሰዎች ሁሉ አምላካዊ ካልሆነው ተግባራቸው ጋር ይሖዋ እንደሚፈርድባቸው ተንብዮአል። ሄኖክ የአምላክ ፍርዶች ያላንዳች ጥርጥር እንደሚፈጸሙ እርግጠኛ ስለነበር ገና ከመፈጸማቸው በፊት እንደተፈጸሙ አድርጎ መናገሩ ትኩረት የሚስብ ነው። ሰዎች መጀመሪያ በሄኖክ በኋላም በኖኅ ላይ አሹፈው ይሆናል፤ ይሁን እንጂ እነዚህ ዘባቾች በሙሉ ምድርን ባጥለቀለቀው ጎርፍ ሰጥመው ጠፍተዋል።
-
-
“ለእምነት በብርቱ ተጋደሉ”!መጠበቂያ ግንብ—1998 | ሰኔ 1
-
-
a አንዳንድ ተመራማሪዎች ይሁዳ ጠቅሶ የጻፈው መጽሐፈ ሄኖክ ከተባለው የአዋልድ መጽሐፍ ነው በማለት ይከራከራሉ። ይሁን እንጂ አር ሲ ኤች ሌንስኪ እንዲህ ብለዋል:- “‘መጽሐፈ ሄኖክ የተባለው መጽሐፍ ምንጩ ከየት ነው?’ ብለን እንጠይቅ ይሆናል። መጽሐፉ ባዕድ ጭማሪ ሲሆን የተለያዩ ክፍሎች መቼ እንደተጻፉ በእርግጠኝነት የሚያውቅ ማንም የለም። . . . ምናልባት አንዳንዶቹ መግለጫዎች ከራሱ ከይሁዳ አልተወሰዱ ይሆናል፤ ሆኖም ማንም ሰው እንዲህ ብሎ በእርግጠኝነት ሊናገር አይችልም።”
-