-
ድል አድራጊ ለመሆን መጣጣርራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
3. (ሀ) ኢየሱስ ለሰምርኔስ ክርስቲያኖች ምን ማበረታቻ ሰጥቶ ነበር? (ለ) በሰምርኔስ የነበሩት ክርስቲያኖች ድሆች ቢሆኑም “ባለ ጠጎች” እንደሆኑ ኢየሱስ የተናገረው ለምን ነበር?
3 “መከራህንና ድህነትህን አውቃለሁ፣ ነገር ግን ባለ ጠጋ ነህ፤ የሰይጣንም ማህበር ናቸው እንጂ አይሁድ ሳይሆኑ:- አይሁድ ነን የሚሉት የሚሳደቡትን ስድብ አውቃለሁ።” (ራእይ 2:9) ኢየሱስ በሰምርኔስ የነበሩትን ወንድሞቹን ሞቅ ባለ ሰሜት ከማመስገን በስተቀር የሚወቅስበት ምክንያት አልነበረውም። በእምነታቸው ምክንያት ብዙ መከራ ደርሶባቸዋል። በታማኝነታቸው ምክንያት ይመስላል፣ ቁሳዊ ሀብት አልነበራቸውም። (ዕብራውያን 10:34) ይሁን እንጂ ዋናው ጭንቀታቸው ለመንፈሳዊ ነገሮች ነበር። ኢየሱስ እንደመከረው በሰማይ መዝገብ አከማችተዋል። (ማቴዎስ 6:19, 20) በዚህም ምክንያት ዋነኛው እረኛ “ባለ ጠጋ” እንደሆኑ አድርጎ ይመለከታቸዋል።—ከያዕቆብ 2:5 ጋር አወዳድር።
4. በሰምርኔስ የነበሩት ክርስቲያኖች ከፍተኛ ተቃውሞ የደረሰባቸው ከእነማን ነበር? ኢየሱስ እነዚህን ተቃዋሚዎች እንዴት ይመለከታቸው ነበር?
4 ኢየሱስ የሰምርኔስ ክርስቲያኖች በተለይ ከሥጋውያን አይሁዶች ብዙ ተቃውሞ እንደ ደረሰባቸው ተናግሮአል። በቀደሙት ዘመናት ብዙዎቹ የዚህ ሃይማኖት አባሎች የክርስትናን መስፋፋት ተቃውመው ነበር። (ሥራ 13:44, 45፤ 14:19) አሁን ደግሞ ኢየሩሳሌም ከወደመች ከጥቂት ዓመታት በኋላ በሰምርኔስ የነበሩት አይሁዶች ይህንኑ ሰይጣናዊ መንፈስ አሳይተዋል። ኢየሱስ “የሰይጣን ማህበር ናቸው” ማለቱ አያስደንቅም።a
-
-
ድል አድራጊ ለመሆን መጣጣርራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
a ዮሐንስ ከሞተ ከ60 ዓመታት ያህል ጊዜ በኋላ የ86 ዓመት ሽማግሌ የነበረው ፖሊካርፕ በኢየሱስ ላይ የነበረውን እምነት ለመካድ አሻፈረኝ በማለቱ በሰምርኔስ ከተማ በእሳት ተቃጥሎ ተገድሎአል። ይህ ድርጊት በተፈጸመበት ጊዜ የተጻፈ ነው የሚባለው የፖሊካርፕ ሰማዕትነት የተባለው መጽሐፍ እንደሚለው ፖሊካርፕ የተቃጠለበት እንጨት በሚሰበሰብበት ጊዜ “አይሁዳውያን እንደልማዳቸው በታላቅ ቅንዓት እንጨት በመሰብሰብ ሥራ ተካፍለው ነበር።” ፖሊካርፕ የተገደለው “በትልቁ የሰንበት ቀን” መሆኑ እንኳን በዚህ ሥራ እንዳይካፈሉ አላገዳቸውም።
-