-
“ያለህን አጽንተህ ያዝ”ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
10. ኢየሱስ በፊልድልፍያ ለነበረው ጉባኤ ምን ማበረታቻ ሰጥቶአል?
10 ኢየሱስ በፊልድልፍያ ለነበሩት ክርስቲያኖች የተናገረው ቃል እንዲህ ካለ ታላቅ ባለ ሥልጣን የመጣ ስለሆነ በጣም ሳያጽናናቸው አልቀረም። ኢየሱስ እንዲህ ሲል አመሰገናቸው:- “ሥራህን አውቃለሁ እነሆ፣ በአንተ ፊት የተከፈተ በር ሰጥቼአለሁ። ማንም ሊዘጋው አይችልም ኃይልህ ምንም ትንሽ ቢሆን ቃሌን ጠብቀሃልና፣ ስሜንም አልካድህምና።” (ራእይ 3:8) ጉባኤው ለሥራ ሲንቀሳቀስ የቆየ ስለሆነ ማንም ሊዘጋው የማይችል በር ተከፍቶለታል። ይህም የአገልግሎት አጋጣሚ በር መሆኑ አያጠራጥርም። (ከ1 ቆሮንቶስ 16:9ና ከ2 ቆሮንቶስ 2:12 ጋር አወዳድር።) ስለዚህ ጉባኤው ባገኘው የስብከት አጋጣሚ ሙሉ በሙሉ እንዲጠቀም ኢየሱስ አበረታቶታል። ጸንተው ስለተገኙ በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ በይሖዋ አገልግሎት ተጨማሪ ሥራ ለመፈጸም የሚያስችል ኃይል እንዳላቸው አረጋግጠዋል። (2 ቆሮንቶስ 12:10፤ ዘካርያስ 4:6) የኢየሱስን ትዕዛዝ ፈጽመዋል፣ በአንደበታቸውም ሆነ በድርጊታቸው ክርስቶስን አልካዱም።
-
-
“ያለህን አጽንተህ ያዝ”ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
14. ኢሳይያስ 49:23 እና ዘካርያስ 8:23 በዘመናችን በጉልህ የተፈጸሙት እንዴት ነው?
14 በዘመናችንም እንደ ኢሳይያስ 49:23 እና ዘካርያስ 8:23 የመሰሉት ትንቢቶች በጉልህ ሁኔታ ተፈጽመዋል። የዮሐንስ ክፍል አባሎች ባከናወኑት የስብከት ሥራ ምክንያት በጣም ብዙ ሰዎች በተከፈተው በር በኩል ወደ መንግሥቱ አገልግሎት ገብተዋል።b ከእነዚህ ሰዎች አብዛኞቹ የመጡት በሐሰት መንፈሣዊ እሥራኤል ነኝ ከምትለው ከሕዝበ ክርስትና ነው። (ከሮሜ 9:6 ጋር አወዳድር።) እነዚህ ሰዎች የእጅግ ብዙ ሰዎች ክፍል እንደመሆናቸው መጠን በኢየሱስ ቤዛዊ ደም በማመን ልብሳቸውን አጥበው አንጽተዋል። (ራእይ 7:9, 10, 14) የክርስቶስን ንጉሣዊ አገዛዝ ስለሚታዘዙ የዚህችን መንግሥት በረከት በዚህችው ምድር ላይ ለመውረስ ተስፋ ያደርጋሉ። አምላክ ከኢየሱስ ቅቡዓን ወንድሞች ጋር እንዳለ ስለ ሰሙ በመንፈሳዊ አባባል ወደ እነርሱ ሄደው ይሰግዱላቸዋል። እነዚህን በምድር አቀፍ የወንድማማችነት ማህበር የተባበሩአቸውን ቅቡዓን ክርስቲያኖች ያገለግሉአቸዋል።—ማቴዎስ 25:34-40፤ 1 ጴጥሮስ 5:9
-
-
“ያለህን አጽንተህ ያዝ”ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
b በዮሐንስ ክፍል የሚታተመው መጠበቂያ ግንብ መጽሔት በዚህ አጋጣሚ መጠቀምና በተቻለ መጠን በስብከቱ ሥራ መካፈል በጣም አጣዳፊ መሆኑን ሲያስገነዝብ ቆይቶአል። ለምሳሌ ያህል፣ በጥር 1, 2004 መጠበቂያ ግንብ እትም ላይ “ሰው ሁሉ የይሖዋን ክብር ያውጅ” እና “‘ድምፃቸው በምድር ሁሉ ላይ ወጣ’” በሚሉ ርዕሶች የቀረቡትን ትምህርቶች ተመልከት። በሰኔ 1, 2004 እትም ላይ “ለአምላክ ክብር የሚሰጡ የተባረኩ ናቸው” በሚል ርዕስ በቀረበው ትምህርት ላይ ‘በተከፈተው በር’ ወደ ሙሉ ጊዜ አገልግሎት መግባት በጣም አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል። በ2005 በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ 1,093,552 የደረሰ ከፍተኛ የአቅኚዎች ቁጥር ሪፖርት ተደርጓል።
-