-
የአምላክ መንግሥት—ከሁሉ የላቀ መስተዳድርመጠበቂያ ግንብ—2006 | ሐምሌ 15
-
-
ኢየሱስና ተባባሪ ገዢዎቹ ከፍ ባለ ቦታ ሆነው ይገዛሉ። ዳንኤል ‘መንግሥትና ሥልጣን ለቅዱሳኑ ሲሰጥ’ በራእይ ተመልክቷል። (ዳንኤል 7:27) ኢየሱስ የሚገዛው ብቻውን አይደለም። ከእርሱ ጋር ነገሥታት ሆነው የሚገዙና ካህናት ሆነው የሚያገለግሉ ሌሎች ሰዎችም አሉ። (ራእይ 5:9, 10፤ 20:6) እነዚህን በተመለከተ ሐዋርያው ዮሐንስ እንዲህ በማለት ጽፏል:- “አየሁ፤ እነሆ፤ በጉ በጽዮን ተራራ ላይ ቆሞ ነበር፤ ከእርሱም ጋር . . . [ከምድር የተዋጁ] መቶ አርባ አራቱ ሺህ ሰዎች ነበሩ።”—ራእይ 14:1-3
በጉ፣ የአምላክ መንግሥት ንጉሥ ሆኖ የተሾመው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። (ዮሐንስ 1:29፤ ራእይ 22:3) የጽዮን ተራራ ደግሞ ሰማይን ያመለክታል።a (ዕብራውያን 12:22) ኢየሱስና 144,000 ተባባሪ ገዢዎቹ ከፍ ባለ ቦታ ይኸውም በሰማይ ሆነው እየገዙ ነው። በሰማይ በመሆናቸው ሁሉንም ነገር ለማየት ይችላሉ። ‘የእግዚአብሔር መንግሥት’ መቀመጫው ሰማይ በመሆኑ “መንግሥተ ሰማይ” በመባልም ተጠርቷል። (ሉቃስ 8:10፤ ማቴዎስ 13:11) ማንኛውም የጦር መሣሪያም ሆነ የኑክሌር ጥቃት በሰማይ ያለውን መንግሥት ሊያሰጋውም ሆነ ሊያጠፋው አይችልም። ፈጽሞ የማይናወጥ ከመሆኑም በላይ የይሖዋን ዓላማ ዳር ያደርሳል።—ዕብራውያን 12:28
-
-
የአምላክ መንግሥት—ከሁሉ የላቀ መስተዳድርመጠበቂያ ግንብ—2006 | ሐምሌ 15
-
-
a የጥንቷ እስራኤል ንጉሥ የነበረው ዳዊት ኢያቡሳውያንን ድል አድርጎ ምድራዊውን የጽዮን ተራራ በመያዝ ዋና ከተማው አድርጓታል። (2 ሳሙኤል 5:6, 7, 9) ቅዱሱንም ታቦት ወደ ጽዮን አዛውሮታል። (2 ሳሙኤል 6:17) ታቦቱ የይሖዋን መገኘት ያመለክት ስለነበር ጽዮን የአምላክ ማደሪያ እንደሆነች ተደርጋ ተገልጻለች፤ ይህም ለሰማይ ተስማሚ ምሳሌ እንድትሆን አድርጓታል።—ዘፀአት 25:22፤ ዘሌዋውያን 16:2፤ መዝሙር 9:11፤ ራእይ 11:19
-