-
በሕዝበ ክርስትና ላይ የሚወርደው የይሖዋ መቅሠፍትራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
29. ‘እንደ መብራት የሚነደው’ ትልቅ ኮከብ ምሳሌ የሆነው ለማን ነው? ለምንስ?
29 ከዚህ ቀደም ኢየሱስ ለሰባቱ ጉባኤዎች በላከው መልእክት ኮከብ የጉባኤ ሽማግሌዎችን እንደሚያመለክት ተመልክተን ነበር።b (ራእይ 1:20) ቅቡዓን “ኮከቦች” ከሌሎች ቅቡዓን ክርስቲያኖች ጋር ሆነው ሰማያዊ ውርሻ የማግኘታቸው ምሳሌ የሆነውን የመንፈስ ቅዱስ ማኅተም ከተቀበሉበት ጊዜ ጀምሮ የሚኖሩት በመንፈሳዊ አነጋገር በሰማይ ነው። (ኤፌሶን 2:6, 7) ይሁን እንጂ ከእነዚህ ኮከብ መሰል ሰዎች መካከል መንጋውን የሚያስቱ መናፍቃንና ከሃዲዎች እንደሚነሱ ሐዋርያው ጳውሎስ አስጠንቅቆ ነበር። (ሥራ 20:29, 30) እንዲህ ያለው የታማኝነት ጉድለት ትልቅ ክህደት ያስከትላል። እነዚህ የወደቁ ሽማግሌዎች እንደ አንድ አካል በመሆን ራሱን በሰው ልጆች መካከል በአምላክ ደረጃ ላይ ያስቀመጠው የዓመፅ ሰው ክፍል ይሆናሉ። (2 ተሰሎንቄ 2:3, 4) የሕዝበ ክርስትና ቀሳውስት በምድር መድረክ ላይ ብቅ ባሉ ጊዜ የጳውሎስ ማስጠንቀቂያ ተፈጽሞአል። ይህ የቀሳውስት ቡድን “እንደ ችቦ የሚቃጠል ታላቅ ኮከብ” በሚል ምሳሌ መጠራቱ ተገቢ ነው።
-
-
በሕዝበ ክርስትና ላይ የሚወርደው የይሖዋ መቅሠፍትራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
b በኢየሱስ እጅ ውስጥ የነበሩት ሰባት ከዋክብት በክርስቲያን ጉባኤ ውስጥ የነበሩ ቅቡዓን የበላይ ተመልካቾችን የሚያመለክቱ ቢሆንም በአሁኑ ጊዜ በምድር በሙሉ በሚገኙት ከ100,000 የሚበልጡ ጉባኤዎች ውስጥ የሚገኙት የበላይ ተመልካቾች የእጅግ ብዙ ሰዎች ክፍል ናቸው። (ራእይ 1:16፤ 7:9) ታዲያ የእነዚህ ደረጃ ምንድን ነው? ሹመታቸውን ያገኙት በተቀባው ታማኝና ልባም ባሪያ አማካኝነት ከመንፈስ ቅዱስ ስለሆነ እነርሱም በኢየሱስ ቀኝ እጅ ቁጥጥር ሥር ያሉ የበታች እረኞች ናቸው። (ኢሳይያስ 61:5, 6፤ ሥራ 20:28) ብቃት ያላቸው ቅቡዓን በማይገኙባቸው ቦታዎች ሁሉ ስለሚያገለግሉ ‘ለሰባቱ ከዋክብት’ ድጋፍ ይሰጣሉ።
-