የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w18 ጥር ገጽ 32
  • ይህን ያውቁ ኖሯል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ይህን ያውቁ ኖሯል?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ይሖዋ ደስ የሚሰኝበት አገልጋይ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
  • “የይሖዋ ሕግ ፍጹም ነው”
    ወደ ይሖዋ ቅረብ
  • ‘ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ምርጤ!’
    የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
w18 ጥር ገጽ 32

ይህን ያውቁ ኖሯል?

በሙሴ ሕግ ውስጥ ያሉት መሠረታዊ ሥርዓቶች በጥንቷ እስራኤል በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ ለሚያጋጥሙ ክርክሮች እልባት ለመስጠት ይሠራባቸው ነበር?

አዎ፣ አንዳንድ ጊዜ ይሠራባቸው ነበር። አንድ ምሳሌ እንመልከት። ዘዳግም 24:14, 15 እንዲህ ይላል፦ “ከወንድሞችህም ሆነ በምድርህ . . . ውስጥ ከሚኖሩ የባዕድ አገር ሰዎች መካከል የተቸገረውንና ድሃ የሆነውን ቅጥር ሠራተኛ አታታል። . . . አለዚያ በአንተ የተነሳ ወደ ይሖዋ ይጮኻል፤ አንተም በኃጢአት ትጠየቃለህ።”

የሸክላ ስብርባሪ

የእርሻ ሠራተኛው አቤቱታ የተጻፈበት የሸክላ ስብርባሪ

አንድ ሰው እንዲህ ያለ ሁኔታ ባጋጠመው ጊዜ ያቀረበውን አቤቱታ የያዘ በሰባተኛው መቶ ዘመን ዓ.ዓ. የተዘጋጀ ሰነድ ተገኝቷል። ሰነዱ የተገኘው በአሽዶድ አቅራቢያ ነው። ጽሑፉ የሰፈረው በሸክላ ስብርባሪ ላይ ሲሆን ሐሳቡ፣ የሚጠበቅበትን የእህል መጠን አላስረከበም የተባለን አንድ የእርሻ ሠራተኛ የሚመለከት ነው፤ ሰነዱ እንዲህ ይላል፦ “አገልጋይህ [አቤቱታ አቅራቢው] ከጥቂት ቀናት በፊት ምርቱን አስገብቶ ከጨረሰ በኋላ የሾባይ ልጅ የሆነው ሆሻያሁ መጣና የአገልጋይህን ልብስ ወሰደበት። . . . በጠራራ ፀሐይ ከእኔ ጋር አዝመራውን ሲያጭዱ የነበሩት ጓደኞቼ በሙሉ . . . የተናገርኩት እውነት እንደሆነ ይመሠክራሉ። ምንም ጥፋት የለብኝም። . . . ገዢው የአገልጋዩን ልብስ የማስመለስ ግዴታ እንዳለበት ባይሰማው እንኳ [ለእኔ] ለአገልጋዩ በመራራት ይህን ያድርግልኝ! አገልጋይህ ልብሱ ተወስዶበት እያለ ዝም ማለት የለብህም።”

ሳይመን ሻማ የተባሉት የታሪክ ምሁር እንዲህ ብለዋል፦ “[ይህ አቤቱታ]፣ አንድ ቅጥር ሠራተኛ . . . [ልብሱን] ለማስመለስ ምን ያህል እንደተጨነቀ የሚያሳይ ብቻ አይደለም። አቤቱታ አቅራቢው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለሚገኘው ሕግ፣ በተለይም በዘሌዋውያንና በዘዳግም ላይ ስለሰፈሩትና ድሆችን መበደልን ስለሚያወግዙት ትእዛዛት የሚያውቀው ነገር እንደነበረም [ሰነዱ] ይጠቁማል።”

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ