-
መስከረም 28 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራምየመንግሥት አገልግሎት—2015 | መስከረም
-
-
መስከረም 28 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
መስከረም 28 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 73 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 25 ከአን. 1-7፣ በገጽ 199 እና 200 ላይ የሚገኙት ሣጥኖች (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ 2 ነገሥት 23-25 (8 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ 2 ነገሥት 23:8-15 (3 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ መላእክት በአምላክ ዓላማ ውስጥ ምን ሚና አላቸው?—የቃላት መፍቻ፣ nwt ከገጽ 1625-1626 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ አልዓዛር—ጭብጥ፦ ይሖዋን በድፍረት አገልግሉት—w98 12/15 ገጽ 12 አን. 13 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
የወሩ ጭብጥ፦ ‘ምሥራቹን በተሟላ ሁኔታ መሥክሩ።’—ሥራ 20:24
10 ደቂቃ፦ ጳውሎስና የአገልግሎት ጓደኞቹ በፊልጵስዩስ የተሟላ ምሥክርነት ሰጡ። በውይይት የሚቀርብ። የሐዋርያት ሥራ 16:11-15 እንዲነበብ አድርግ። ከዚያም ይህ ዘገባ ከአገልግሎታችን ጋር በተያያዘ ሊጠቅመን የሚችለው እንዴት እንደሆነ ተወያዩበት።
20 ደቂቃ፦ “ምሥራች በተባለው ብሮሹር ተጠቅሞ ማስጠናት።” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። በአንቀጽ 3 ላይ ከተወያያችሁ በኋላ አንድ አስፋፊ ምሥራች የተባለውን ብሮሹር ሲያበረክትና በአንድ አንቀጽ ላይ ሲወያይ የሚያሳይ ጥሩ ዝግጅት የተደረገበት ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
መዝሙር 114 እና ጸሎት
-
-
ምሥራች በተባለው ብሮሹር ተጠቅሞ ማስጠናትየመንግሥት አገልግሎት—2015 | መስከረም
-
-
1. ምሥራች የተባለው ብሮሹር የተዘጋጀው በምን መንገድ ነው?
1 በሐምሌ የመንግሥት አገልግሎታችን ላይ እንደተገለጸው አዘውትረን ከምንጠቀምባቸው የማስተማሪያ መሣሪያዎቻችን መካከል አንዱ ከአምላክ የተላከ ምሥራች! የተባለው ብሮሹር ነው። ጥቅሶቹ ምዕራፍና ቁጥራቸው ብቻ መጠቀሳቸው የምናነጋግረው ሰው በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ እንዲያነብ ያስችለዋል። አብዛኞቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ማስጠኛ ጽሑፎቻችን የተዘጋጁት ግለሰቡ ጽሑፎቹን በግሉም ለማጥናት በሚያስችለው መንገድ ነው፤ ይህ ብሮሹር የተዘጋጀው ግን ከአንድ አስጠኚ ጋር በውይይት እንዲጠና ተደርጎ ነው። በመሆኑም ብሮሹሩን ስናበረክት እንዴት እንደሚጠና ማሳየታችን የምናነጋግረው ግለሰብ መጽሐፍ ቅዱስ የያዘውን ምሥራች መማር በጣም አስደሳች መሆኑን እንዲገነዘብ ሊረዳው ይችላል።—ማቴ. 13:44
-