የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • gf ትምህርት 1 ገጽ 3
  • አምላክ ወዳጁ እንድትሆን ይጋብዝሃል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አምላክ ወዳጁ እንድትሆን ይጋብዝሃል
  • የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የይሖዋ ወዳጅ መሆን ትችላለህ
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
  • የጓደኛዬን ስህተት መናገር ይኖርብኛል?
    ንቁ!—2008
  • ምን ይመስልሃል?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2018
  • መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ጓደኝነት ምን ይላል?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
ለተጨማሪ መረጃ
የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
gf ትምህርት 1 ገጽ 3

ትምህርት 1

አምላክ ወዳጁ እንድትሆን ይጋብዝሃል

አምላክ ወዳጁ እንድትሆን ይፈልጋል። በአጽናፈ ዓለሙ ውስጥ ከሁሉም በላይ ታላቅ ከሆነው አካል ጋር ወዳጅ መሆን እንደምትችል አስበህ ታውቃለህ? ጥንት ይኖር የነበረው አብርሃም የአምላክ ወዳጅ ተብሎ ተጠርቷል። (ያዕቆብ 2:23) በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ ሌሎች ሰዎችም የአምላክ ወዳጅ የነበሩ ሲሆን በብዙ ተባርከዋል። ዛሬ በተለያዩ የምድር ክፍሎች የሚኖሩ ሰዎችም ከአምላክ ጋር ወዳጅነትን መሥርተዋል። አንተም የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ።

አብርሃም ሲጸልይ

የአምላክ ወዳጅ መሆን ከማንም ሰው ጋር ከመወዳጀት የሚበልጥ ነው። አምላክ ታማኝ ወዳጆቹን ፈጽሞ አያስቀይማቸውም። (መዝሙር 18:25፣ የ1980 ትርጉም) የአምላክ ወዳጅ መሆን ባለጠጋ ከመሆን የተሻለ ነው። ባለጠጋ የሆነ ሰው ሲሞት ገንዘቡን ሌሎች ሰዎች ይወስዱታል። የአምላክ ወዳጅ የሆኑ ግን ማንም ሊወስደው የማይችለው ሃብት አላቸው።—ማቴዎስ 6:19

አንዳንድ ሰዎች ስለ አምላክ መማርህን እንድታቆም ለማድረግ ሊሞክሩ ይችላሉ። አንዳንድ ጓደኞችህና የቤተሰብህ አባሎች እንዲህ ሊያደርጉ ይችላሉ። (ማቴዎስ 10:36, 37) ሰዎች ቢስቁብህ ወይም ቢያስፈራሩህ እንዲህ ብለህ ራስህን ጠይቅ:- ‘ማስደሰት የምፈልገው ማንን ነው? ሰዎችን ወይስ አምላክን?’ እስቲ አስበው:- አንድ ሰው ምግብ እንዳትበላ ቢከለክልህ እሺ ብለህ ትታዘዘዋለህ? እሺ እንደማትለው የታወቀ ነው! ለመኖር ምግብ መመገብ ይኖርብሃል። አምላክ ደግሞ ለዘላለም እንድትኖር ሊያደርግ ይችላል! ስለዚህ የአምላክ ወዳጅ መሆን ስለምትችልበት መንገድ የምታደርገውን ጥናት ማንም ሰው እንዲያስቆምህ አትፍቀድ።—ዮሐንስ 17:3

ስለ አምላክ የሚያወሳ ጽሑፍ የምታነብን ሴት ሰዎች ሲቀልዱባት
    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ