የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • gf ትምህርት 2 ገጽ 4
  • አምላክ ከማንም የሚበልጥ ወዳጅ ነው

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አምላክ ከማንም የሚበልጥ ወዳጅ ነው
  • የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የይሖዋ ወዳጅ መሆን ትችላለህ
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
  • ከይሖዋ ጋር ያለህ ተራ ትውውቅ ነው ወይስ ወዳጅነት?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1992
  • አምላክ ወዳጁ እንድትሆን ይጋብዝሃል
    የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
  • ወዳጆች ማፍራት የምትችለው እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2000
ለተጨማሪ መረጃ
የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
gf ትምህርት 2 ገጽ 4

ትምህርት 2

አምላክ ከማንም የሚበልጥ ወዳጅ ነው

አንዲት ሴት መጽሐፍ ቅዱስን ስታነብ

የአምላክ ወዳጅ መሆን ልታገኝ ከምትችለው ነገር ሁሉ የሚበልጥ ነው። አምላክ ደስተኛና የተረጋጋ ሕይወት እንዴት መምራት እንደምትችል ያስተምርሃል። ከተሳሳቱ እምነቶችና ከጎጂ ልማዶች ነፃ ያደርግሃል። የምታቀርበውን ጸሎት ይሰማል። ውስጣዊ ሰላምና ትምክህት እንዲኖርህ ይረዳሃል። (መዝሙር 71:5፤ 73:28) አምላክ በመከራ ጊዜ ይደግፍሃል። (መዝሙር 18:18) እንዲሁም የዘላለም ሕይወት ስጦታ ይሰጥሃል።—ሮሜ 6:23

አንዲት ሴት የአምላክ ወዳጅ ከሆነ ቤተሰብ ጋር ስትገናኝ

ወደ አምላክ ይበልጥ እየቀረብክ በሄድክ መጠን ከአምላክ ወዳጆች ጋርም እንደዚያው እየተቀራረብህ ትሄዳለህ። እነርሱም የአንተ ወዳጆች ይሆናሉ። እንዲያውም እንደ ወንድሞችህና እህቶችህ ይሆኑልሃል። አንተን ስለ አምላክ ለማስተማር፣ ለመርዳትና ለማበረታታት ደስተኞች ናቸው።

ከአምላክ ጋር እኩል አይደለንም። የአምላክ ወዳጅ ለመሆን በምትፈልግበት ጊዜ አንድ አስፈላጊ ሃቅ መገንዘብ አለብህ። ከአምላክ ጋር ወዳጅ መሆን እኩያ በሆኑ ሁለት አካላት መካከል ከሚኖረው ወዳጅነት ጋር አንድ ዓይነት አይደለም። እርሱ ከእኛ ይልቅ ብዙ ዕድሜ ያለው ከመሆኑም በላይ ከእኛ የላቀ ጥበብና ኃይል አለው። እርሱ ገዥያችን ለመሆን መብት ያለው ነው። ስለዚህ የእርሱ ወዳጆች መሆን ከፈለግን እርሱን ማዳመጥና እንድናደርግ የሚያስተምረንን ሁሉ በተግባር ማዋል አለብን። እንዲህ ማድረጋችን ምንጊዜም ጥቅም ያስገኝልናል።—ኢሳይያስ 48:18

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ