የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • yp1 ገጽ 149
  • አርዓያ የሚሆኑ ሰዎች—ሙሴ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አርዓያ የሚሆኑ ሰዎች—ሙሴ
  • ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 1
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • እምነት በማሳየት ረገድ ሙሴን ምሰሉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2014
  • ሙሴ የእምነት ሰው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2013
  • የይሖዋን መንገድ መማር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
  • ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ሙሴ ያለ ነቢይ የነበረው እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1991
ለተጨማሪ መረጃ
ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 1
yp1 ገጽ 149

አርዓያ የሚሆኑ ሰዎች—ሙሴ

ሙሴ ጥሩ የሚባል ሕይወት ለመምራት የሚያስችሉ አጋጣሚዎች ነበሩት። ሙሴ ያደገው በፈርዖን ቤተ መንግሥት ሲሆን የግብፃውያንን ጥበብ ሁሉ ተምሮ ነበር። (የሐዋርያት ሥራ 7:22) ታዲያ ይህን ሥልጠና እንዴት ይጠቀምበት ይሆን? ሙሴ በቀሰመው ትምህርት ተጠቅሞ ዝና ማትረፍ፣ ሀብት ማካበት እንዲሁም ሥልጣን ማግኘት ይችል ነበር። እሱ ግን እነዚህን ነገሮች በማሳደድ ላይ አላተኮረም፤ በእኩዮች ተጽዕኖም አልተሸነፈም። ሙሴ ያደረገው ምርጫ ብዙዎችን የሚያስገርም ነው። “ከአምላክ ሕዝብ ጋር መንገላታትን” መርጧል። (ዕብራውያን 11:25) ሙሴ እንዲህ ያለ ምርጫ በማድረጉ የቀረበት ነገር አለ? በፍጹም። አምላክን ለማገልገል እና ሰዎችን ለመርዳት በመምረጡ አስደሳችና የሚያረካ ሕይወት መምራት ችሏል።

አንተም ጥሩ ትምህርት የማግኘት አጋጣሚ ካለህ የቀሰምከውን እውቀት የምትጠቀምበት እንዴት ነው? እውቀትህን ሀብት ለማካበት ወይም ሥልጣን ለማግኘት ልትጠቀምበት ትችል ይሆናል። ወይም ደግሞ ልክ እንደ ሙሴ በሕይወትህ ውስጥ ትርጉም ያለው ነገር ለማከናወን ልትመርጥ ትችላለህ። እውቀትህንና ችሎታህን ተጠቅመህ አምላክን ማገልገል እና ሌሎችን መርዳት ትችላለህ። (ማቴዎስ 22:35-40) ደግሞም ከዚህ ይበልጥ እርካታ የሚያስገኝ ነገር የለም!

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ