የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 10
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኢሳይያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • በእስራኤል ላይ የተዘረጋው የአምላክ እጅ (1-4)

      • አሦር፣ የአምላክ የቁጣ በትር (5-11)

      • በአሦር ላይ የሚደርስ ቅጣት (12-19)

      • ከያዕቆብ ቤት የሚተርፉት ይመለሳሉ (20-27)

      • አምላክ በአሦር ላይ ይፈርዳል (28-34)

ኢሳይያስ 10:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 19:15፤ ዘዳ 1:16, 17

ኢሳይያስ 10:2

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ወላጅ አልባ የሆኑ ልጆችን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +አሞጽ 2:7, 8
  • +ዘዳ 27:19፤ ያዕ 1:27

ኢሳይያስ 10:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በምትቀጡበት።”

  • *

    ወይም “ክብራችሁንስ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሆሴዕ 9:7
  • +ዘዳ 28:49, 50
  • +ሆሴዕ 5:13

ኢሳይያስ 10:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 5:25፤ 9:12

ኢሳይያስ 10:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 17:3፤ ኢሳ 8:3, 4፤ 10:24
  • +ዘፍ 10:9, 11

ኢሳይያስ 10:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 17:6
  • +ዘዳ 28:45, 63፤ 2ነገ 17:22, 23

ኢሳይያስ 10:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 18:19, 24

ኢሳይያስ 10:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +አሞጽ 6:2
  • +2ዜና 35:20
  • +2ነገ 17:24
  • +2ነገ 19:11, 13
  • +2ነገ 17:5፤ 18:9, 10
  • +2ነገ 16:8, 9

ኢሳይያስ 10:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 19:17, 18

ኢሳይያስ 10:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 18:33, 34፤ 2ዜና 32:16, 19

ኢሳይያስ 10:12

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “እቀጣዋለሁ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 18:19, 28, 35

ኢሳይያስ 10:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 15:29፤ 17:6፤ 18:11፤ 1ዜና 5:26
  • +2ነገ 16:8፤ 18:16
  • +2ነገ 18:19, 25

ኢሳይያስ 10:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 10:5

ኢሳይያስ 10:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 32:21
  • +ኢሳ 30:30, 31

ኢሳይያስ 10:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 84:11
  • +ኢሳ 9:5፤ 30:27፤ 31:8, 9፤ ናሆም 1:6

ኢሳይያስ 10:18

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ከነፍስ እስከ ሥጋ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 37:36

ኢሳይያስ 10:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 28:20, 21፤ ሆሴዕ 5:13፤ 14:3

ኢሳይያስ 10:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 65:9፤ ሆሴዕ 1:10, 11

ኢሳይያስ 10:22

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ቅጣትም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 1:9
  • +ኢሳ 28:22
  • +ሮም 9:27, 28

ኢሳይያስ 10:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 28:45, 63

ኢሳይያስ 10:24

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 18:13፤ ኢሳ 10:5
  • +ዘፀ 14:3, 9

ኢሳይያስ 10:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 19:35

ኢሳይያስ 10:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መሳ 7:25፤ 8:21፤ መዝ 83:11
  • +2ዜና 32:21፤ ኢሳ 30:32፤ ናሆም 3:7
  • +ዘፀ 14:21, 27

ኢሳይያስ 10:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 9:4፤ ናሆም 1:13
  • +ኢሳ 14:25
  • +2ነገ 19:35፤ ኢሳ 37:35, 36

ኢሳይያስ 10:28

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢያሱ 7:2
  • +1ሳሙ 13:2፤ 14:31

ኢሳይያስ 10:29

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወንዝ ማቋረጥ የሚቻልበት ጥልቀት የሌለው የወንዝ ክፍል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢያሱ 21:8, 17፤ 2ዜና 16:6
  • +መሳ 20:13
  • +ሆሴዕ 5:8

ኢሳይያስ 10:30

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢያሱ 21:8, 18፤ ኤር 1:1

ኢሳይያስ 10:32

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 22:18, 19

ኢሳይያስ 10:33

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 32:21፤ ኢሳ 37:36

ኢሳይያስ 10:34

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በመጥረቢያ።”

ተዛማጅ ሐሳብ

ኢሳ. 10:1ዘሌ 19:15፤ ዘዳ 1:16, 17
ኢሳ. 10:2አሞጽ 2:7, 8
ኢሳ. 10:2ዘዳ 27:19፤ ያዕ 1:27
ኢሳ. 10:3ሆሴዕ 9:7
ኢሳ. 10:3ዘዳ 28:49, 50
ኢሳ. 10:3ሆሴዕ 5:13
ኢሳ. 10:4ኢሳ 5:25፤ 9:12
ኢሳ. 10:52ነገ 17:3፤ ኢሳ 8:3, 4፤ 10:24
ኢሳ. 10:5ዘፍ 10:9, 11
ኢሳ. 10:62ነገ 17:6
ኢሳ. 10:6ዘዳ 28:45, 63፤ 2ነገ 17:22, 23
ኢሳ. 10:82ነገ 18:19, 24
ኢሳ. 10:9አሞጽ 6:2
ኢሳ. 10:92ዜና 35:20
ኢሳ. 10:92ነገ 17:24
ኢሳ. 10:92ነገ 19:11, 13
ኢሳ. 10:92ነገ 17:5፤ 18:9, 10
ኢሳ. 10:92ነገ 16:8, 9
ኢሳ. 10:102ነገ 19:17, 18
ኢሳ. 10:112ነገ 18:33, 34፤ 2ዜና 32:16, 19
ኢሳ. 10:122ነገ 18:19, 28, 35
ኢሳ. 10:132ነገ 15:29፤ 17:6፤ 18:11፤ 1ዜና 5:26
ኢሳ. 10:132ነገ 16:8፤ 18:16
ኢሳ. 10:132ነገ 18:19, 25
ኢሳ. 10:15ኢሳ 10:5
ኢሳ. 10:162ዜና 32:21
ኢሳ. 10:16ኢሳ 30:30, 31
ኢሳ. 10:17መዝ 84:11
ኢሳ. 10:17ኢሳ 9:5፤ 30:27፤ 31:8, 9፤ ናሆም 1:6
ኢሳ. 10:18ኢሳ 37:36
ኢሳ. 10:202ዜና 28:20, 21፤ ሆሴዕ 5:13፤ 14:3
ኢሳ. 10:21ኢሳ 65:9፤ ሆሴዕ 1:10, 11
ኢሳ. 10:22ኢሳ 1:9
ኢሳ. 10:22ኢሳ 28:22
ኢሳ. 10:22ሮም 9:27, 28
ኢሳ. 10:23ዘዳ 28:45, 63
ኢሳ. 10:242ነገ 18:13፤ ኢሳ 10:5
ኢሳ. 10:24ዘፀ 14:3, 9
ኢሳ. 10:252ነገ 19:35
ኢሳ. 10:26መሳ 7:25፤ 8:21፤ መዝ 83:11
ኢሳ. 10:262ዜና 32:21፤ ኢሳ 30:32፤ ናሆም 3:7
ኢሳ. 10:26ዘፀ 14:21, 27
ኢሳ. 10:27ኢሳ 9:4፤ ናሆም 1:13
ኢሳ. 10:27ኢሳ 14:25
ኢሳ. 10:272ነገ 19:35፤ ኢሳ 37:35, 36
ኢሳ. 10:28ኢያሱ 7:2
ኢሳ. 10:281ሳሙ 13:2፤ 14:31
ኢሳ. 10:29ኢያሱ 21:8, 17፤ 2ዜና 16:6
ኢሳ. 10:29መሳ 20:13
ኢሳ. 10:29ሆሴዕ 5:8
ኢሳ. 10:30ኢያሱ 21:8, 18፤ ኤር 1:1
ኢሳ. 10:321ሳሙ 22:18, 19
ኢሳ. 10:332ዜና 32:21፤ ኢሳ 37:36
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
  • 32
  • 33
  • 34
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኢሳይያስ 10:1-34

ኢሳይያስ

10 ጉዳት የሚያስከትሉ ሥርዓቶችን የሚያወጡ፣+

ሁልጊዜ ጨቋኝ ድንጋጌዎችን የሚያረቁ ወዮላቸው!

 2 የድሆችን አቤቱታ ላለመስማት፣

በሕዝቤም መካከል የሚገኙትን ምስኪኖች ፍትሕ ለመንፈግ ሕግ የሚያወጡ ወዮላቸው!+

መበለቶችን ይበዘብዛሉ፤

አባት የሌላቸውንም ልጆች* ይዘርፋሉ።+

 3 በምትመረመሩበት* ቀን፣+

ጥፋትም ከሩቅ በሚመጣበት ጊዜ ምን ይውጣችሁ ይሆን?+

እርዳታ ለማግኘት ወደ ማን ትሸሻላችሁ?+

ሀብታችሁንስ* የት ትተዉት ይሆን?

 4 በእስረኞች መካከል ተኮራምታችሁ ከመቀመጥና

በሞቱ ሰዎች መካከል ከመውደቅ በስተቀር የምታተርፉት ነገር የለም።

ከዚህ ሁሉ የተነሳ ቁጣው አልተመለሰም፤

ይልቁንም እጁ ለመምታት ገና እንደተዘረጋ ነው።+

 5 “የቁጣዬ በትር የሆነውንና+

ውግዘቴን የምገልጽበትን ዱላ በእጁ የያዘውን

አሦራዊ+ ተመልከት!

 6 ከሃዲ በሆነው ብሔር ላይ፣

እጅግ ባስቆጣኝም ሕዝብ ላይ እልከዋለሁ፤+

ብዙ ምርኮ እንዲወስድ፣ ብዙ ሀብት እንዲዘርፍና

ሕዝቡን በጎዳናዎች ላይ እንዳለ ጭቃ እንዲረጋግጥ አዘዋለሁ።+

 7 እሱ ግን እንዲህ ያለ ዝንባሌ አይኖረውም፤

ልቡም እንዲህ ለማድረግ አያቅድም፤

የልቡ ፍላጎት መደምሰስና

ጥቂት ሳይሆን ብዙ ብሔራትን ማጥፋት ነውና።

 8 እሱ እንዲህ ይላል፦

‘አለቆች ሆነው የሚያገለግሉኝ ሁሉ ነገሥታት አይደሉም?+

 9 ካልኖ+ እንደ ካርከሚሽ+ አይደለችም?

ሃማት+ እንደ አርጳድ+ አይደለችም?

ሰማርያስ+ እንደ ደማስቆ+ አይደለችም?

10 እጄ በኢየሩሳሌምና በሰማርያ ካሉት ይበልጥ በርካታ የተቀረጹ ምስሎች ያሏቸውንና

ከንቱ አማልክት የሚያመልኩትን መንግሥታት ይዟል!+

11 በሰማርያና ከንቱ በሆኑት አማልክቷ ላይ እንዳደረግኩት ሁሉ፣

በኢየሩሳሌምና በጣዖቶቿስ ላይ እንዲሁ አላደርግም?’+

12 “ይሖዋ በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም የሚያከናውነውን ሥራ ሁሉ ሲያጠናቅቅ በእብሪተኛ ልቡ፣ በኩራቱና በትዕቢተኛ ዓይኑ የተነሳ የአሦርን ንጉሥ ይቀጣዋል።*+ 13 እሱ እንዲህ ይላልና፦

‘በእጄ ብርታትና በጥበቤ

ይህን አደርጋለሁ፤ እኔ ጥበበኛ ነኝና።

የሕዝቦችን ድንበር አስወግዳለሁ፤+

ሀብታቸውንም እዘርፋለሁ፤+

እንደ ኃያል ሰውም ነዋሪዎቹን በቁጥጥር ሥር አውላለሁ።+

14 ሰው እጁን ወደ ወፍ ጎጆ እንደሚሰድ፣

እጄ የሕዝቦችን ሀብት ይይዛል፤

አንድ ሰው የተተዉ እንቁላሎችን እንደሚሰበስብ

እኔም መላውን ምድር እሰበስባለሁ!

ክንፎቹን የሚያራግብ ወይም አፉን የሚከፍት አሊያም የሚጮኽ አይኖርም።’”

15 መጥረቢያ፣ በሚቆርጥበት ሰው ላይ ይኩራራል?

መጋዝ፣ በሚገዘግዝበት ሰው ላይ ራሱን ከፍ ከፍ ያደርጋል?

በትር፣+ የሚያነሳውን ሰው ወዲያና ወዲህ ማንቀሳቀስ ይችላል?

ወይስ ዱላ፣ ከእንጨት ያልተሠራውን ሰው ወደ ላይ ከፍ ማድረግ ይችላል?

16 ስለዚህ እውነተኛው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ

በወፈሩት ሰዎች ላይ ክሳትን ይሰዳል፤+

ከክብሩም በታች እንደ እሳት ነበልባል የሚንቦገቦግ እሳት ያነዳል።+

17 የእስራኤል ብርሃን+ እንደ እሳት፣+

ቅዱስ አምላኩም እንደ ነበልባል ይሆናል፤

አረሙንና ቁጥቋጦውን በአንድ ቀን ያጋየዋል፤ ደግሞም ይበላዋል።

18 አምላክ የደኑንና የፍራፍሬ እርሻውን ክብር ፈጽሞ* ያጠፋል፤

ክብሩም እንደታመመ ሰው እየመነመነ ይሄዳል።+

19 በደኑ ውስጥ የሚተርፉት ዛፎች

ጥቂት ከመሆናቸው የተነሳ አንድ ትንሽ ልጅ ቆጥሮ ሊመዘግባቸው ይችላል።

20 በዚያ ቀን ከእስራኤላውያን መካከል የሚቀሩት፣

ከያዕቆብም ቤት የሚተርፉት ሰዎች

ከእንግዲህ ወዲህ፣ በመታቸው ላይ ፈጽሞ አይታመኑም፤+

ከዚህ ይልቅ የእስራኤል ቅዱስ በሆነው በይሖዋ ላይ

በታማኝነት ይደገፋሉ።

21 ጥቂት ቀሪዎች ይኸውም ከያዕቆብ ቤት የሚተርፉት ሰዎች

ወደ ኃያሉ አምላክ ይመለሳሉ።+

22 እስራኤል ሆይ፣

ሕዝብህ እንደ ባሕር አሸዋ ቢሆንም

ከእነሱ መካከል ጥቂት ቀሪዎች ይመለሳሉ።+

ጥፋት ተወስኗል፤+

ፍትሕም* ይውጣቸዋል።+

23 አዎ፣ ሉዓላዊው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ የወሰነው ጥፋት፣

በመላ ምድሪቱ ላይ ይፈጸማል።+

24 ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “በጽዮን የምትኖር ሕዝቤ ሆይ፣ በበትር+ ይመታህና ግብፅ እንዳደረገብህ+ ዱላውን በአንተ ላይ ያነሳ የነበረውን አሦርን አትፍራ። 25 ከጥቂት ጊዜ በኋላ ውግዘቱ ያበቃልና፤ ቁጣዬም እስኪጠፉ ድረስ በእነሱ ላይ ይነድዳል።+ 26 የሠራዊት ጌታ ይሖዋ በኦሬብ ዓለት ምድያምን ድል እንዳደረገ+ ሁሉ ጅራፉን በእሱ ላይ ያወዛውዛል።+ በትሩም በባሕሩ ላይ ይሆናል፤ በግብፅ ላይ እንዳደረገውም በትሩን ያነሳዋል።+

27 “በዚያ ቀን ሸክሙ ከትከሻህ ላይ፣+

ቀንበሩም ከአንገትህ ላይ ይወርዳል፤+

ከዘይቱም የተነሳ ቀንበሩ ይሰበራል።”+

28 በአያት+ ላይ መጥቷል፤

ሚግሮንን አቋርጦ አልፏል፤

በሚክማሽ+ ጓዙን ያስቀምጣል።

29 መልካውን* ተሻግረዋል፤

በጌባ+ ያድራሉ፤

ራማ ራደች፤ የሳኦል ከተማ ጊብዓ+ ሸሽታለች።+

30 የጋሊም ሴት ልጅ ሆይ፣ እሪታሽን አቅልጪው!

ላይሻ ሆይ፣ አዳምጪ!

ምስኪኗ አናቶት+ ሆይ፣ ጩኺ!

31 ማድመና ሸሽታለች።

የጌቢም ነዋሪዎች መሸሸጊያ ፈለጉ።

32 በዚሁ ቀን በኖብ+ ያርፋል።

በጽዮን ሴት ልጅ ተራራ፣

በኢየሩሳሌም ኮረብታ ላይ እጁን በዛቻ ያወዛውዛል።

33 እነሆ፣ እውነተኛው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ

ቅርንጫፎችን በታላቅ ኃይል እየቆራረጠ ይጥላል፤+

ረጃጅሞቹ ዛፎች ይገነደሳሉ፤

ከፍ ያሉትም ይዋረዳሉ።

34 በደን ውስጥ ያለውን ጥሻ በብረት መሣሪያ* ይቆራርጣል፤

ሊባኖስም በኃያሉ እጅ ይወድቃል።

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ