ኢሳይያስ
10 ጉዳት የሚያስከትሉ ሥርዓቶችን የሚያወጡ፣+
ሁልጊዜ ጨቋኝ ድንጋጌዎችን የሚያረቁ ወዮላቸው!
2 የድሆችን አቤቱታ ላለመስማት፣
በሕዝቤም መካከል የሚገኙትን ምስኪኖች ፍትሕ ለመንፈግ ሕግ የሚያወጡ ወዮላቸው!+
መበለቶችን ይበዘብዛሉ፤
4 በእስረኞች መካከል ተኮራምታችሁ ከመቀመጥና
በሞቱ ሰዎች መካከል ከመውደቅ በስተቀር የምታተርፉት ነገር የለም።
ከዚህ ሁሉ የተነሳ ቁጣው አልተመለሰም፤
ይልቁንም እጁ ለመምታት ገና እንደተዘረጋ ነው።+
6 ከሃዲ በሆነው ብሔር ላይ፣
እጅግ ባስቆጣኝም ሕዝብ ላይ እልከዋለሁ፤+
ብዙ ምርኮ እንዲወስድ፣ ብዙ ሀብት እንዲዘርፍና
ሕዝቡን በጎዳናዎች ላይ እንዳለ ጭቃ እንዲረጋግጥ አዘዋለሁ።+
7 እሱ ግን እንዲህ ያለ ዝንባሌ አይኖረውም፤
ልቡም እንዲህ ለማድረግ አያቅድም፤
የልቡ ፍላጎት መደምሰስና
ጥቂት ሳይሆን ብዙ ብሔራትን ማጥፋት ነውና።
8 እሱ እንዲህ ይላል፦
‘አለቆች ሆነው የሚያገለግሉኝ ሁሉ ነገሥታት አይደሉም?+
10 እጄ በኢየሩሳሌምና በሰማርያ ካሉት ይበልጥ በርካታ የተቀረጹ ምስሎች ያሏቸውንና
ከንቱ አማልክት የሚያመልኩትን መንግሥታት ይዟል!+
11 በሰማርያና ከንቱ በሆኑት አማልክቷ ላይ እንዳደረግኩት ሁሉ፣
በኢየሩሳሌምና በጣዖቶቿስ ላይ እንዲሁ አላደርግም?’+
12 “ይሖዋ በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም የሚያከናውነውን ሥራ ሁሉ ሲያጠናቅቅ በእብሪተኛ ልቡ፣ በኩራቱና በትዕቢተኛ ዓይኑ የተነሳ የአሦርን ንጉሥ ይቀጣዋል።*+ 13 እሱ እንዲህ ይላልና፦
‘በእጄ ብርታትና በጥበቤ
ይህን አደርጋለሁ፤ እኔ ጥበበኛ ነኝና።
14 ሰው እጁን ወደ ወፍ ጎጆ እንደሚሰድ፣
እጄ የሕዝቦችን ሀብት ይይዛል፤
አንድ ሰው የተተዉ እንቁላሎችን እንደሚሰበስብ
እኔም መላውን ምድር እሰበስባለሁ!
ክንፎቹን የሚያራግብ ወይም አፉን የሚከፍት አሊያም የሚጮኽ አይኖርም።’”
15 መጥረቢያ፣ በሚቆርጥበት ሰው ላይ ይኩራራል?
መጋዝ፣ በሚገዘግዝበት ሰው ላይ ራሱን ከፍ ከፍ ያደርጋል?
በትር፣+ የሚያነሳውን ሰው ወዲያና ወዲህ ማንቀሳቀስ ይችላል?
ወይስ ዱላ፣ ከእንጨት ያልተሠራውን ሰው ወደ ላይ ከፍ ማድረግ ይችላል?
19 በደኑ ውስጥ የሚተርፉት ዛፎች
ጥቂት ከመሆናቸው የተነሳ አንድ ትንሽ ልጅ ቆጥሮ ሊመዘግባቸው ይችላል።
20 በዚያ ቀን ከእስራኤላውያን መካከል የሚቀሩት፣
ከያዕቆብም ቤት የሚተርፉት ሰዎች
ከእንግዲህ ወዲህ፣ በመታቸው ላይ ፈጽሞ አይታመኑም፤+
ከዚህ ይልቅ የእስራኤል ቅዱስ በሆነው በይሖዋ ላይ
በታማኝነት ይደገፋሉ።
21 ጥቂት ቀሪዎች ይኸውም ከያዕቆብ ቤት የሚተርፉት ሰዎች
ወደ ኃያሉ አምላክ ይመለሳሉ።+
23 አዎ፣ ሉዓላዊው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ የወሰነው ጥፋት፣
በመላ ምድሪቱ ላይ ይፈጸማል።+
24 ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “በጽዮን የምትኖር ሕዝቤ ሆይ፣ በበትር+ ይመታህና ግብፅ እንዳደረገብህ+ ዱላውን በአንተ ላይ ያነሳ የነበረውን አሦርን አትፍራ። 25 ከጥቂት ጊዜ በኋላ ውግዘቱ ያበቃልና፤ ቁጣዬም እስኪጠፉ ድረስ በእነሱ ላይ ይነድዳል።+ 26 የሠራዊት ጌታ ይሖዋ በኦሬብ ዓለት ምድያምን ድል እንዳደረገ+ ሁሉ ጅራፉን በእሱ ላይ ያወዛውዛል።+ በትሩም በባሕሩ ላይ ይሆናል፤ በግብፅ ላይ እንዳደረገውም በትሩን ያነሳዋል።+
30 የጋሊም ሴት ልጅ ሆይ፣ እሪታሽን አቅልጪው!
ላይሻ ሆይ፣ አዳምጪ!
ምስኪኗ አናቶት+ ሆይ፣ ጩኺ!
31 ማድመና ሸሽታለች።
የጌቢም ነዋሪዎች መሸሸጊያ ፈለጉ።
32 በዚሁ ቀን በኖብ+ ያርፋል።
በጽዮን ሴት ልጅ ተራራ፣
በኢየሩሳሌም ኮረብታ ላይ እጁን በዛቻ ያወዛውዛል።
34 በደን ውስጥ ያለውን ጥሻ በብረት መሣሪያ* ይቆራርጣል፤
ሊባኖስም በኃያሉ እጅ ይወድቃል።