የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ረቡዕ፣ መስከረም 17

የዓመፅ ሥራቸው ይቅር የተባለላቸው፣ ኃጢአታቸውም የተሸፈነላቸው ደስተኞች ናቸው።—ሮም 4:7

አምላክ በእሱ የሚያምኑ ሰዎችን ኃጢአታቸውን ይሰርዝላቸዋል ወይም ይሸፍንላቸዋል። ሙሉ በሙሉ ይቅር ይላቸዋል፤ እንዲሁም ኃጢአታቸውን አይቆጥርባቸውም። (መዝ. 32:1, 2) እንዲህ ያሉትን ሰዎች፣ እምነታቸውን መሠረት በማድረግ ነቀፋ የሌለባቸው ወይም ጻድቃን አድርጎ ይቆጥራቸዋል። አብርሃም፣ ዳዊትና ሌሎች ታማኝ የአምላክ አገልጋዮች ጻድቃን ተደርገው ቢቆጠሩም ፍጽምና የጎደላቸው ኃጢአተኞች ነበሩ። ሆኖም በእምነታቸው ምክንያት አምላክ ነቀፋ የሌለባቸው አድርጎ ቆጥሯቸዋል። በተለይ በእሱ ላይ እምነት ከሌላቸው ሰዎች ጋር ሲወዳደሩ ጻድቃን ተደርገው መቆጠራቸው ተገቢ ነው። (ኤፌ. 2:12) ሐዋርያው ጳውሎስ በደብዳቤው ላይ በግልጽ እንደተናገረው ከአምላክ ጋር የቅርብ ወዳጅነት ለመመሥረት እምነት የግድ አስፈላጊ ነው። አብርሃምና ዳዊት የአምላክ ወዳጅ መሆን የቻሉት እምነት ስለነበራቸው ነው። እኛም ብንሆን የአምላክ ወዳጅ ለመሆን እምነት ያስፈልገናል። w23.12 3 አን. 6-7

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ሐሙስ፣ መስከረም 18

የውዳሴ መሥዋዕት ዘወትር ለአምላክ እናቅርብ፤ ይህም ስሙን በይፋ የምናውጅበት የከንፈራችን ፍሬ ነው።—ዕብ. 13:15

በዛሬው ጊዜ ሁሉም ክርስቲያኖች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ገንዘባቸውን ተጠቅመው ከአምላክ መንግሥት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በማራመድ ለይሖዋ መሥዋዕት የማቅረብ መብት አላቸው። ካሉን ነገሮች መካከል ምርጡን ለይሖዋ መሥዋዕት አድርገን በማቅረብ እሱን የማምለክ መብታችንን ከፍ አድርገን እንደምንመለከተው እናሳያለን። ሐዋርያው ጳውሎስ ፈጽሞ ችላ ልንላቸው የማይገቡ የተለያዩ የአምልኳችንን ገጽታዎች ጠቅሷል። (ዕብ. 10:22-25) ከእነዚህ መካከል ወደ ይሖዋ በጸሎት መቅረብ፣ ተስፋችንን በይፋ ማወጅ፣ በጉባኤ ደረጃ አንድ ላይ መሰብሰብ እንዲሁም “[የይሖዋ ቀን] እየቀረበ መምጣቱን ስናይ ከበፊቱ ይበልጥ” እርስ በርስ መበረታታት ይገኙበታል። በራእይ መጽሐፍ መደምደሚያ አካባቢ የይሖዋ መልአክ ሁለት ጊዜ “ለአምላክ ስገድ!” ብሏል፤ ይህም ይሖዋን የማምለክን አስፈላጊነት ጎላ አድርጎ ያሳያል። (ራእይ 19:10፤ 22:9) ታላቁን የይሖዋ መንፈሳዊ ቤተ መቅደስ አስመልክቶ ያገኘነውን ጥልቅ መንፈሳዊ እውነት እንዲሁም ያለንን ታላቁን አምላካችንን ይሖዋን የማምለክ ውድ መብት ፈጽሞ ልንረሳው አይገባም! w23.10 29 አን. 17-18

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ዓርብ፣ መስከረም 19

እርስ በርስ መዋደዳችንን እንቀጥል።—1 ዮሐ. 4:7

ሁላችንም ‘እርስ በርስ መዋደዳችንን መቀጠል’ እንፈልጋለን። ሆኖም ኢየሱስ “የብዙዎች ፍቅር ይቀዘቅዛል” የሚል ማስጠንቀቂያ እንደሰጠ ማስታወስ ይኖርብናል። (ማቴ. 24:12) ኢየሱስ ይህን ሲል የአብዛኞቹ ደቀ መዛሙርቱ ፍቅር እንደሚቀዘቅዝ መናገሩ አልነበረም። ያም ቢሆን፣ በምንኖርበት ዓለም ውስጥ ፍቅር መጥፋቱ ተጽዕኖ እንዳያሳድርብን ልንጠነቀቅ ይገባል። ይህን ሐሳብ በአእምሯችን በመያዝ የሚከተለውን ጥያቄ ለመመለስ እንሞክር፦ ለወንድሞቻችን ያለን ፍቅር ጠንካራ መሆኑን መፈተን የምንችልበት መንገድ አለ? ፍቅራችን ምን ያህል ጠንካራ እንደሆነ መፈተን የምንችልበት አንዱ መንገድ በሕይወታችን ውስጥ የሚያጋጥሙንን አንዳንድ ሁኔታዎች እንዴት እንደምንይዝ መገምገም ነው። (2 ቆሮ. 8:8) ሐዋርያው ጴጥሮስ ከእነዚህ ሁኔታዎች መካከል አንዱን ሲጠቅስ እንዲህ ብሏል፦ “ከሁሉም በላይ አንዳችሁ ለሌላው የጠለቀ ፍቅር ይኑራችሁ፤ ምክንያቱም ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናል።” (1 ጴጥ. 4:8) በመሆኑም የሌሎች ድክመትና አለፍጽምና ፍቅራችንን ሊፈትነው ይችላል። w23.11 10-11 አን. 12-13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ