የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ሐሙስ፣ መስከረም 18

የውዳሴ መሥዋዕት ዘወትር ለአምላክ እናቅርብ፤ ይህም ስሙን በይፋ የምናውጅበት የከንፈራችን ፍሬ ነው።—ዕብ. 13:15

በዛሬው ጊዜ ሁሉም ክርስቲያኖች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ገንዘባቸውን ተጠቅመው ከአምላክ መንግሥት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በማራመድ ለይሖዋ መሥዋዕት የማቅረብ መብት አላቸው። ካሉን ነገሮች መካከል ምርጡን ለይሖዋ መሥዋዕት አድርገን በማቅረብ እሱን የማምለክ መብታችንን ከፍ አድርገን እንደምንመለከተው እናሳያለን። ሐዋርያው ጳውሎስ ፈጽሞ ችላ ልንላቸው የማይገቡ የተለያዩ የአምልኳችንን ገጽታዎች ጠቅሷል። (ዕብ. 10:22-25) ከእነዚህ መካከል ወደ ይሖዋ በጸሎት መቅረብ፣ ተስፋችንን በይፋ ማወጅ፣ በጉባኤ ደረጃ አንድ ላይ መሰብሰብ እንዲሁም “[የይሖዋ ቀን] እየቀረበ መምጣቱን ስናይ ከበፊቱ ይበልጥ” እርስ በርስ መበረታታት ይገኙበታል። በራእይ መጽሐፍ መደምደሚያ አካባቢ የይሖዋ መልአክ ሁለት ጊዜ “ለአምላክ ስገድ!” ብሏል፤ ይህም ይሖዋን የማምለክን አስፈላጊነት ጎላ አድርጎ ያሳያል። (ራእይ 19:10፤ 22:9) ታላቁን የይሖዋ መንፈሳዊ ቤተ መቅደስ አስመልክቶ ያገኘነውን ጥልቅ መንፈሳዊ እውነት እንዲሁም ያለንን ታላቁን አምላካችንን ይሖዋን የማምለክ ውድ መብት ፈጽሞ ልንረሳው አይገባም! w23.10 29 አን. 17-18

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ዓርብ፣ መስከረም 19

እርስ በርስ መዋደዳችንን እንቀጥል።—1 ዮሐ. 4:7

ሁላችንም ‘እርስ በርስ መዋደዳችንን መቀጠል’ እንፈልጋለን። ሆኖም ኢየሱስ “የብዙዎች ፍቅር ይቀዘቅዛል” የሚል ማስጠንቀቂያ እንደሰጠ ማስታወስ ይኖርብናል። (ማቴ. 24:12) ኢየሱስ ይህን ሲል የአብዛኞቹ ደቀ መዛሙርቱ ፍቅር እንደሚቀዘቅዝ መናገሩ አልነበረም። ያም ቢሆን፣ በምንኖርበት ዓለም ውስጥ ፍቅር መጥፋቱ ተጽዕኖ እንዳያሳድርብን ልንጠነቀቅ ይገባል። ይህን ሐሳብ በአእምሯችን በመያዝ የሚከተለውን ጥያቄ ለመመለስ እንሞክር፦ ለወንድሞቻችን ያለን ፍቅር ጠንካራ መሆኑን መፈተን የምንችልበት መንገድ አለ? ፍቅራችን ምን ያህል ጠንካራ እንደሆነ መፈተን የምንችልበት አንዱ መንገድ በሕይወታችን ውስጥ የሚያጋጥሙንን አንዳንድ ሁኔታዎች እንዴት እንደምንይዝ መገምገም ነው። (2 ቆሮ. 8:8) ሐዋርያው ጴጥሮስ ከእነዚህ ሁኔታዎች መካከል አንዱን ሲጠቅስ እንዲህ ብሏል፦ “ከሁሉም በላይ አንዳችሁ ለሌላው የጠለቀ ፍቅር ይኑራችሁ፤ ምክንያቱም ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናል።” (1 ጴጥ. 4:8) በመሆኑም የሌሎች ድክመትና አለፍጽምና ፍቅራችንን ሊፈትነው ይችላል። w23.11 10-11 አን. 12-13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ቅዳሜ፣ መስከረም 20

እርስ በርሳችሁ [ተዋደዱ]።—ዮሐ. 13:34

በጉባኤው ውስጥ ላሉ አንዳንድ ክርስቲያኖች ፍቅር እያሳየን ለሌሎቹ ግን የማናሳይ ከሆነ ኢየሱስ ስለ ፍቅር የሰጠውን ትእዛዝ ተከትለናል ሊባል አይችልም። እርግጥ ነው፣ እኛም እንደ ኢየሱስ ከአንዳንዶቹ ወንድሞቻችን ጋር ይበልጥ እንቀራረብ ይሆናል። (ዮሐ. 13:23፤ 20:2) ሆኖም ሐዋርያው ጴጥሮስ ለሁሉም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን “የወንድማማች መዋደድ” ማለትም በቤተሰብ ውስጥ ያለው ዓይነት ፍቅር ሊኖረን እንደሚገባ አሳስቦናል። (1 ጴጥ. 2:17) ጴጥሮስ “እርስ በርሳችሁ አጥብቃችሁ ከልብ ተዋደዱ” የሚል ማበረታቻ ሰጥቶናል። (1 ጴጥ. 1:22) ‘አጥብቆ መዋደድ’ የሚለው አገላለጽ ፍቅር ማሳየት በሚከብደን ጊዜም ጭምር መዋደድን ያካትታል። ለምሳሌ አንድ ወንድም ቅር ቢያሰኘን ወይም በሆነ መንገድ ቢጎዳንስ? የሚቀናን ፍቅር ማሳየት ሳይሆን አጸፋውን መመለስ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ጴጥሮስ አጸፋ መመለስ አምላክን እንደማያስደስተው ከኢየሱስ ተምሯል። (ዮሐ. 18:10, 11) ጴጥሮስ “ክፉን በክፉ ወይም ስድብን በስድብ አትመልሱ። ከዚህ ይልቅ ባርኩ” ሲል ጽፏል። (1 ጴጥ. 3:9) ሌሎችን አጥብቀን የምንወድ ከሆነ ደግነትና አሳቢነት ለማሳየት እንነሳሳለን። w23.09 28-29 አን. 9-11

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ