የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 1 ሳሙኤል 11
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

1 ሳሙኤል የመጽሐፉ ይዘት

      • ሳኦል አሞናውያንን ድል መታ (1-11)

      • የሳኦል ንግሥና በድጋሚ ጸና (12-15)

1 ሳሙኤል 11:1

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ስምምነት አድርግ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 2:19
  • +መሳ 21:8፤ 1ሳሙ 31:11, 12

1 ሳሙኤል 11:2

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    12/15/1995፣ ገጽ 9-10

1 ሳሙኤል 11:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 10:26፤ 14:2

1 ሳሙኤል 11:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መሳ 3:9, 10፤ 6:34፤ 11:29፤ 14:5, 6፤ 1ሳሙ 10:10, 11፤ 16:13

1 ሳሙኤል 11:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 11:3

1 ሳሙኤል 11:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ከሌሊቱ 8 ሰዓት እስከ ጠዋት 12 ሰዓት ገደማ ያለውን ጊዜ ያመለክታል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 11:1

1 ሳሙኤል 11:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 10:26, 27

1 ሳሙኤል 11:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 19:22

1 ሳሙኤል 11:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 7:15, 16
  • +1ሳሙ 10:17, 24

1 ሳሙኤል 11:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 7:11
  • +1ነገ 1:39, 40፤ 2ነገ 11:12, 14፤ 1ዜና 12:39, 40

ተዛማጅ ሐሳብ

1 ሳሙ. 11:1ዘዳ 2:19
1 ሳሙ. 11:1መሳ 21:8፤ 1ሳሙ 31:11, 12
1 ሳሙ. 11:41ሳሙ 10:26፤ 14:2
1 ሳሙ. 11:6መሳ 3:9, 10፤ 6:34፤ 11:29፤ 14:5, 6፤ 1ሳሙ 10:10, 11፤ 16:13
1 ሳሙ. 11:101ሳሙ 11:3
1 ሳሙ. 11:111ሳሙ 11:1
1 ሳሙ. 11:121ሳሙ 10:26, 27
1 ሳሙ. 11:132ሳሙ 19:22
1 ሳሙ. 11:141ሳሙ 7:15, 16
1 ሳሙ. 11:141ሳሙ 10:17, 24
1 ሳሙ. 11:15ዘሌ 7:11
1 ሳሙ. 11:151ነገ 1:39, 40፤ 2ነገ 11:12, 14፤ 1ዜና 12:39, 40
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
1 ሳሙኤል 11:1-15

አንደኛ ሳሙኤል

11 ከዚያም አሞናዊው+ ናሃሽ ወጥቶ በጊልያድ የምትገኘውን ኢያቢስን ከበባት። የኢያቢስ+ ሰዎች በሙሉ ናሃሽን “ከእኛ ጋር ቃል ኪዳን ግባ፤* እኛም እናገለግልሃለን” አሉት። 2 አሞናዊው ናሃሽም “ከእናንተ ጋር ቃል ኪዳን የምገባው የእያንዳንዳችሁ ቀኝ ዓይን ከወጣ ነው። ይህን የማደርገውም መላውን እስራኤል ለማዋረድ ስል ነው” አላቸው። 3 የኢያቢስ ሽማግሌዎችም “ወደ መላው የእስራኤል ግዛት መልእክተኞችን እንድንልክ የሰባት ቀን ጊዜ ስጠን። ከዚያም የሚያድነን ሰው ከሌለ ለአንተ እጃችንን እንሰጣለን” ሲሉ መለሱለት። 4 መልእክተኞቹም ሳኦል ወደሚገኝበት ወደ ጊብዓ+ መጥተው ይህን መልእክት ለሕዝቡ ተናገሩ፤ ሕዝቡም ሁሉ ድምፁን ከፍ አድርጎ አለቀሰ።

5 ሳኦል ግን መንጋውን እየነዳ ከመስክ በመምጣት ላይ ነበር፤ ሳኦልም “ሕዝቡ የሚያለቅሰው ምን ሆኖ ነው?” አለ። እነሱም የኢያቢስ ሰዎች ያሏቸውን ነገሩት። 6 ሳኦልም ይህን ሲሰማ የአምላክ መንፈስ ኃይል ሰጠው፤+ ቁጣውም ነደደ። 7 እሱም ጥንድ በሬዎችን ወስዶ ቆራረጣቸው፤ እነዚህንም በመልእክተኞቹ እጅ አስይዞ “ሳኦልንና ሳሙኤልን የማይከተል ማንኛውም ሰው ከብቱ እንዲህ ይቆራረጣል!” በማለት እንዲናገሩ ወደ መላው የእስራኤል ግዛት ላካቸው። በሕዝቡም ላይ የይሖዋ ፍርሃት ስለወደቀ ሕዝቡ እንደ አንድ ሰው ሆኖ ወጣ። 8 ከዚያም ሳኦል ሰዎቹን ቤዜቅ ላይ ቆጠራቸው፤ እነሱም 300,000 እስራኤላውያንና 30,000 የይሁዳ ሰዎች ነበሩ። 9 የመጡትንም መልእክተኞች እንዲህ አሏቸው፦ “በጊልያድ ባለችው በኢያቢስ የሚኖሩትን ሰዎች ‘በነገው ዕለት ፀሐይዋ በምትከርበት ጊዜ መዳን ታገኛላችሁ’ በሏቸው።” ከዚያም መልእክተኞቹ መጥተው ለኢያቢስ ሰዎች ነገሯቸው፤ እነሱም በደስታ ፈነደቁ። 10 ስለሆነም የኢያቢስ ሰዎች “ነገ እጃችንን ለእናንተ እንሰጣለን፤ እናንተም መልካም መስሎ የታያችሁን ሁሉ ልታደርጉብን ትችላላችሁ” አሏቸው።+

11 በማግስቱ ሳኦል ሕዝቡን በሦስት ቡድን ከፈለው፤ እነሱም በማለዳው ክፍለ ሌሊት* ወደ አሞናውያን+ ሰፈር ገብተው ፀሐይዋ እስክትከር ድረስ መቷቸው። የተረፉትም ቢሆኑ ሁለቱ እንኳ አንድ ላይ መሆን እስከማይችሉ ድረስ ተበታተኑ። 12 ከዚያም ሕዝቡ ሳሙኤልን “‘አሁን ሳኦል በእኛ ላይ ንጉሥ ሊሆን ነው?’ ሲሉ የነበሩት እነማን ናቸው?+ እነዚህን ሰዎች ስጡንና እንግደላቸው” አለው። 13 ሳኦል ግን “ይህ ዕለት ይሖዋ እስራኤልን ያዳነበት ስለሆነ በዚህ ቀን ማንም ሰው መገደል የለበትም” አለ።+

14 በኋላም ሳሙኤል ሕዝቡን “ኑ፣ ወደ ጊልጋል+ እንውጣና ንግሥናውን እንደገና እናጽና” አለ።+ 15 በመሆኑም ሕዝቡ ሁሉ ወደ ጊልጋል ሄደ፤ በጊልጋልም ሳኦልን በይሖዋ ፊት አነገሡት። በዚያም በይሖዋ ፊት የኅብረት መሥዋዕቶችን አቀረቡ፤+ ሳኦልና የእስራኤል ሰዎች ሁሉ እጅግ ተደሰቱ።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ