ዮሐንስ 1:51 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 51 ከዚያም “እውነት እውነት እላችኋለሁ፣ ሰማይ ተከፍቶ የአምላክ መላእክት ወደዚያ ሲወጡና የሰው ልጅ ወዳለበት ሲወርዱ ታያላችሁ” አለው።+ ዕብራውያን 1:7 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 7 በተጨማሪም ስለ መላእክት ሲናገር “መላእክቱን መናፍስት፣ አገልጋዮቹን*+ ደግሞ የእሳት ነበልባል ያደርጋል”+ ይላል። ዕብራውያን 1:14 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 14 ሁሉም መዳን የሚወርሱትን እንዲያገለግሉ የሚላኩ ቅዱስ አገልግሎት* የሚያከናውኑ መናፍስት አይደሉም?+