የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘዳግም 28:49-51
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 49 “ይሖዋ ቋንቋውን የማትረዳውን+ በሩቅ ያለን አንድ ብሔር ከምድር ጫፍ አስነስቶ ያመጣብሃል፤+ እሱም እንደ ንስር ተምዘግዝጎ ይወርድብሃል፤+ 50 ይህ ብሔር ለሽማግሌ የማያዝን ወይም ለወጣት የማይራራ ፊቱ የሚያስፈራ ብሔር ነው።+ 51 እስክትጠፋም ድረስ የእንስሶችህን ግልገልና የምድርህን ፍሬ ይበላሉ። አንተንም እስኪያጠፉህ ድረስ ምንም እህል፣ አዲስ የወይን ጠጅም ሆነ ዘይት፣ ጥጃም ሆነ የበግ ግልገል አያስተርፉልህም።+

  • ኤርምያስ 5:15-17
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 15 “የእስራኤል ቤት ሆይ፣ እነሆ፣ በሩቅ ቦታ ያለን ብሔር አመጣባችኋለሁ”+ ይላል ይሖዋ።

      “እሱም ለረጅም ጊዜ የኖረ ብሔር ነው።

      ከጥንት ዘመን ጀምሮ የነበረ፣

      ቋንቋውን የማታውቀውና

      ንግግሩን የማትረዳው ብሔር ነው።+

      16 የፍላጻ ኮሮጇቸው እንደተከፈተ መቃብር ነው፤

      ሁሉም ተዋጊዎች ናቸው።

      17 እነሱ አዝመራህንና ምግብህን ይበላሉ።+

      ወንዶችና ሴቶች ልጆችህን ይበላሉ።

      መንጎችህንና ከብቶችህን ይበላሉ።

      የወይን ተክሎችህንና የበለስ ዛፎችህን ይበላሉ።

      የምትታመንባቸውን የተመሸጉ ከተሞችህን በሰይፍ ያወድማሉ።”

  • ኤርምያስ 6:22, 23
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 22 ይሖዋ እንዲህ ይላል፦

      “እነሆ፣ ከሰሜን ምድር አንድ ሕዝብ እየመጣ ነው፤

      ከምድር ዳርቻም ታላቅ ብሔር ይነሳል።+

      23 ቀስትና ጦር ይይዛሉ።

      ጨካኝና ምሕረት የለሽ ናቸው።

      ድምፃቸው እንደ ባሕር ያስተጋባል፤

      ፈረሶችንም ይጋልባሉ።+

      የጽዮን ሴት ልጅ ሆይ፣ ልክ እንደ ተዋጊ በአንቺ ላይ ይሰለፋሉ።”

  • ሕዝቅኤል 23:22, 23
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 22 “ስለዚህ ኦሆሊባ ሆይ፣ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘ተጸይፈሽ* የራቅሻቸውን ፍቅረኞችሽን በአንቺ ላይ አስነሳለሁ፤+ እነሱንም ከየአቅጣጫው አመጣብሻለሁ፤+ 23 እነሱም የባቢሎን ልጆችና+ ከለዳውያን+ ሁሉ እንዲሁም የአሦርን ልጆች ሁሉ ጨምሮ የጰቆድ፣+ የሾአ እና የቆአ ሰዎች ናቸው። ሁሉም መልከ ቀና ወጣቶች፣ ገዢዎችና የበታች ገዢዎች፣ ተዋጊዎችና የተመረጡ አማካሪዎች እንዲሁም ፈረሰኞች ናቸው።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ