የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፍጥረት 34
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘፍጥረት የመጽሐፉ ይዘት

      • ዲና ተደፈረች (1-12)

      • የያዕቆብ ወንዶች ልጆች የተንኮል ድርጊት ፈጸሙ (13-31)

ዘፍጥረት 34:1

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በዚያ አገር ያሉ ወጣት ሴቶችን ለማየት።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 30:19, 21፤ 46:15
  • +ዘፍ 26:34, 35፤ 27:46

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    8/1/2001፣ ገጽ 20

    2/1/1997፣ ገጽ 30

ዘፍጥረት 34:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 7:1፤ 1ዜና 1:13-15

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    በአምላክ ፍቅር ኑሩ፣ ገጽ 123-124

    ከአምላክ ፍቅር፣ ገጽ 102-103

ዘፍጥረት 34:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሱ።”

  • *

    ቃል በቃል “ለወጣቷ ልብ ተናገረ።”

ዘፍጥረት 34:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 33:18, 19

ዘፍጥረት 34:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዕብ 13:4
  • +2ሳሙ 13:22

ዘፍጥረት 34:8

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የልጄ የሴኬም ነፍስ ከልጃችሁ ጋር ተጣብቋል።”

ዘፍጥረት 34:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 24:2, 3

ዘፍጥረት 34:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 24:53፤ ሆሴዕ 3:2

ዘፍጥረት 34:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 17:9, 12

ዘፍጥረት 34:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 17:10

ዘፍጥረት 34:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 33:18, 19
  • +ዘፍ 34:2

ዘፍጥረት 34:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 34:15

ዘፍጥረት 34:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘካ 8:16

ዘፍጥረት 34:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 34:8, 9

ዘፍጥረት 34:22

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 17:11

ዘፍጥረት 34:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 46:15
  • +ዘፍ 49:5-7

ዘፍጥረት 34:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 34:2

ዘፍጥረት 34:30

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “እንድገለል አደረጋችሁኝ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 49:5

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    1/15/2004፣ ገጽ 28

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘፍ. 34:1ዘፍ 30:19, 21፤ 46:15
ዘፍ. 34:1ዘፍ 26:34, 35፤ 27:46
ዘፍ. 34:2ዘዳ 7:1፤ 1ዜና 1:13-15
ዘፍ. 34:4ዘፍ 33:18, 19
ዘፍ. 34:7ዕብ 13:4
ዘፍ. 34:72ሳሙ 13:22
ዘፍ. 34:9ዘፍ 24:2, 3
ዘፍ. 34:12ዘፍ 24:53፤ ሆሴዕ 3:2
ዘፍ. 34:14ዘፍ 17:9, 12
ዘፍ. 34:15ዘፍ 17:10
ዘፍ. 34:18ዘፍ 33:18, 19
ዘፍ. 34:18ዘፍ 34:2
ዘፍ. 34:19ዘፍ 34:15
ዘፍ. 34:20ዘካ 8:16
ዘፍ. 34:21ዘፍ 34:8, 9
ዘፍ. 34:22ዘፍ 17:11
ዘፍ. 34:25ዘፍ 46:15
ዘፍ. 34:25ዘፍ 49:5-7
ዘፍ. 34:27ዘፍ 34:2
ዘፍ. 34:30ዘፍ 49:5
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘፍጥረት 34:1-31

ዘፍጥረት

34 ያዕቆብ ከሊያ የወለዳት ዲና+ የተባለችው ልጅ እዚያ አገር ካሉ ወጣት ሴቶች ጋር ጊዜ ለማሳለፍ* ትወጣ ነበር።+ 2 የአገሩ አለቃ የሆነው የሂዋዊው+ የኤሞር ልጅ ሴኬም ዲናን አያት፤ ከዚያም ወሰዳትና አብሯት ተኛ፤ አስገድዶም ደፈራት። 3 እሱም ልቡ* በያዕቆብ ልጅ በዲና ተማረከ፤ ወጣቷንም አፈቀራት፤ በሚያባብሉ ቃላትም አነጋገራት።* 4 በመጨረሻም ሴኬም አባቱን ኤሞርን+ “ከዚህች ልጅ ጋር አጋባኝ” አለው።

5 ያዕቆብ፣ ሴኬም ልጁን ዲናን እንዳስነወራት በሰማ ጊዜ ወንዶች ልጆቹ በመስክ መንጎቹን እየጠበቁ ነበር። በመሆኑም ያዕቆብ ልጆቹ እስኪመለሱ ድረስ ዝም አለ። 6 በኋላም የሴኬም አባት ኤሞር ከያዕቆብ ጋር ለመነጋገር ወጣ። 7 ሆኖም የያዕቆብ ወንዶች ልጆች ስለ ሁኔታው ሰሙ፤ ወዲያውኑም ከመስክ መጡ። ሴኬም የያዕቆብን ሴት ልጅ በመድፈር ፈጽሞ መደረግ የማይገባውን ድርጊት ስለፈጸመና+ በዚህም እስራኤልን ስላዋረደ በጣም ተበሳጩ፤ እጅግም ተቆጡ።+

8 ኤሞርም እንዲህ አላቸው፦ “ልጄ ሴኬም ልጃችሁን በጣም ወዷታል።* እባካችሁ ሚስት እንድትሆነው ስጡት፤ 9 በጋብቻም እንዛመድ። ሴቶች ልጆቻችሁን ዳሩልን፤ የእኛንም ሴቶች ልጆች አግቡ።+ 10 አብራችሁንም መኖር ትችላላችሁ፤ አገራችን አገራችሁ ናት። ኑሩባት፤ ነግዱባት፤ ሀብትም አፍሩባት።” 11 ከዚያም ሴኬም አባቷንና ወንድሞቿን እንዲህ አላቸው፦ “በፊታችሁ ሞገስ ላግኝ እንጂ የምትጠይቁኝን ሁሉ እሰጣለሁ። 12 ብዙ ጥሎሽና ስጦታ ልትጠይቁኝ ትችላላችሁ።+ እኔ የጠየቃችሁኝን ሁሉ ለመስጠት ፈቃደኛ ነኝ። ብቻ ይህችን ወጣት ሚስቴ እንድትሆን ስጡኝ።”

13 የያዕቆብ ወንዶች ልጆችም ሴኬም እህታቸውን ዲናን ስላስነወረ ለእሱና ለአባቱ ለኤሞር ተንኮል ያዘለ መልስ ሰጧቸው። 14 እንዲህም አሏቸው፦ “እንዲህ ያለ ነገር ፈጽሞ አናደርግም፤ እህታችንን ላልተገረዘ ሰው አንሰጥም፤+ ምክንያቱም ይህ ለእኛ ውርደት ነው። 15 በሐሳባችሁ የምንስማማው እኛን ከመሰላችሁና የእናንተ የሆነው ወንድ ሁሉ እንዲገረዝ ካደረጋችሁ ብቻ ነው።+ 16 ከዚያም ሴቶች ልጆቻችንን እንድርላችኋለን፤ እኛም ሴቶች ልጆቻችሁን እናገባለን፤ አብረናችሁም እንኖራለን፤ አንድ ሕዝብም እንሆናለን። 17 የምንላችሁን የማትሰሙና ለመገረዝ ፈቃደኛ የማትሆኑ ከሆነ ግን ልጃችንን ይዘን እንሄዳለን።”

18 የተናገሩትም ነገር ኤሞርንና+ ልጁን ሴኬምን+ ደስ አሰኛቸው። 19 ወጣቱም ያሉትን ነገር ለማድረግ ጊዜ አልወሰደበትም፤+ ምክንያቱም የያዕቆብን ልጅ ወዷት ነበር፤ ደግሞም በአባቱ ቤት ካሉት ሰዎች ሁሉ እጅግ የተከበረ ነበር።

20 በመሆኑም ኤሞርና ልጁ ሴኬም ወደ ከተማዋ በር በመሄድ በከተማቸው የሚኖሩትን ወንዶች+ እንዲህ አሏቸው፦ 21 “እነዚህ ሰዎች ከእኛ ጋር በሰላም መኖር ይፈልጋሉ። ምድሪቱ ለእነሱም ስለምትበቃ በምድሪቱ ይኑሩ፤ እንዲሁም ይነግዱ። ሴቶች ልጆቻቸውን ማግባት፣ የእኛንም ሴቶች ልጆች ለእነሱ መዳር እንችላለን።+ 22 ሆኖም ሰዎቹ ከእኛ ጋር አንድ ሕዝብ በመሆን አብረውን ለመኖር የሚስማሙት፣ ልክ እነሱ እንደተገረዙት የእኛ የሆኑ ወንዶች ሁሉ የሚገረዙ ከሆነ ብቻ ነው።+ 23 እንዲህ ብናደርግ ንብረታቸው፣ ሀብታቸውና ከብቶቻቸው ሁሉ የእኛ ሆኑ ማለት አይደለም? በመሆኑም ከእኛ ጋር ለመኖር ባቀረቡት ሐሳብ እንስማማ።” 24 በከተማው በር የሚወጡ ሁሉ ኤሞርና ልጁ ሴኬም ያሏቸውን ሰሙ፤ በከተማዋም በር የሚወጡ ወንዶች በሙሉ ተገረዙ።

25 ሆኖም በሦስተኛው ቀን፣ ሰዎቹ ገና ቆስለው እያሉ የዲና ወንድሞች+ የሆኑት ሁለቱ የያዕቆብ ልጆች ማለትም ስምዖንና ሌዊ ማንም ሳይጠረጥራቸው ሰይፋቸውን ይዘው ወደ ከተማዋ በመግባት ወንዶቹን ሁሉ ገደሉ።+ 26 ኤሞርንና ልጁን ሴኬምን በሰይፍ ገደሏቸው፤ ከዚያም ዲናን ከሴኬም ቤት ይዘው ሄዱ። 27 ሌሎቹ የያዕቆብ ወንዶች ልጆችም በሬሳ ላይ እየተረማመዱ ከተማዋን ዘረፉ፤ ይህን ያደረጉትም እህታቸው ስለተነወረች ነው።+ 28 እነሱም መንጎቻቸውን፣ ከብቶቻቸውን፣ አህዮቻቸውን እንዲሁም በከተማዋ ውስጥና በመስክ ያገኙትን ሁሉ ወሰዱ። 29 በተጨማሪም ንብረቶቻቸውን በሙሉ ወሰዱ፤ እንዲሁም ትናንሽ ልጆቻቸውንና ሚስቶቻቸውን ማረኩ፤ በየቤቱ ያገኙትን ሁሉ ዘረፉ።

30 በዚህ ጊዜ ያዕቆብ፣ ስምዖንንና ሌዊን+ እንዲህ አላቸው፦ “በዚህች አገር በሚኖሩት በከነአናውያንና በፈሪዛውያን ዘንድ እንደ ጥምብ እንድቆጠር በማድረግ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ከተታችሁኝ።* እኔ እንግዲህ በቁጥር አነስተኛ ነኝ፤ እነሱም በእኔ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ግንባር ፈጥረው መምጣታቸው አይቀርም፤ በዚህም የተነሳ እኔም ሆንኩ ቤቴ እንጠፋለን።” 31 እነሱ ግን “ታዲያ ማንም እህታችንን እንደ ዝሙት አዳሪ ቆጥሮ እንዲህ ያለ ድርጊት ይፈጽምባት?” አሉ።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ