ገጽ ሁለት
ጥያቄው ማጨስ ወይም አለማጨስ ነው። ይህ ጥያቄ የሚደቀንባችሁ አብዛኛውን ጊዜ በወጣትነት ዕድሜያችሁ ነው። ምንም ዓይነት ግዳጅ ውስጥ የማያስገባ በነፃ ምርጫ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ ነው። ይሁን እንጂ የሕክምና ሊቃውንት እንደሚሉት በጤንነታችሁ ላይ ከባድ ውጤት ሊያስከትል ይችላል። እንዲያውም የአሟሟታችሁ ሁኔታና ጊዜ የሚወሰንበት ጥያቄ ሊሆን ይችላል።
ስለዚህ የሚከተሉት አስፈላጊ ጥያቄዎች ይነሳሉ። የትንባሆ ምርቶችን ማስተዋወቅ በሥነ ምግባር ረገድ ትክክል ነውን? ክርስቲያን ናቸው የሚባሉት ብሔራት የትንባሆ ምርቶቻቸውን ወደ ሌሎች አገሮች ልከው ማራገፋቸው ትክክለኛ አድራጎት ሆኖ ሊታይ የሚችልበት ምክንያት ይኖራልን? ሲጋራ ሻጮች የሞትና የበሽታ ነጋዴዎች ናቸውን? ሰዎች ሲጋራ የሚያጨሱት በራሳቸው ምርጫ በመሆኑ ስለ እነዚህ ጥያቄዎች ማሰቡ አስፈላጊ ይሆናልን?