የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • gf ትምህርት 15 ገጽ 24-25
  • የአምላክ ወዳጆች መልካም የሆነውን ያደርጋሉ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአምላክ ወዳጆች መልካም የሆነውን ያደርጋሉ
  • የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ቤተሰብህ ደስተኛ ሊሆን የሚችለው እንዴት ነው?
    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምረናል?
  • ትዳርን ዘላቂ ለማድረግ የሚረዱ ሁለት ቁልፍ ነገሮች
    ለቤተሰብ ደስታ ቁልፉ ምንድን ነው?
  • አምላክን የሚያስደስት የቤተሰብ ሕይወት
    አምላክ ከእኛ የሚፈልገው ምንድን ነው?
  • ለሥልጣን አክብሮት ማሳየት ያለብን ለምንድን ነው?
    ከአምላክ ፍቅር ሳትወጡ ኑሩ
ለተጨማሪ መረጃ
የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
gf ትምህርት 15 ገጽ 24-25

ትምህርት 15

የአምላክ ወዳጆች መልካም የሆነውን ያደርጋሉ

የምታደንቀውና የምታከብረው ወዳጅ ካለህ እርሱን ለመምሰል ትጥራለህ። መጽሐፍ ቅዱስ “እግዚአብሔር ቸር [“ጥሩ፣” NW] ቅንም ነው” በማለት ይናገራል። (መዝሙር 25:8) የአምላክ ወዳጅ ለመሆን ጥሩና ቅን መሆን አለብን። “እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ [“የምትመስሉ፣” NW] ሁኑ” በማለት መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። (ኤፌሶን 5:1, 2) ይህን ከምናደርግባቸው መንገዶች አንዳንዶቹ የሚከተሉት ናቸው:-

ሁለት ሰዎች የግንባታ ሥራ ሲያከናውኑ

ሌሎችን እርዳ። “ለሰው ሁሉ . . . መልካም እናድርግ።”—ገላትያ 6:10

ጠንክረህ ሥራ። “የሰረቀ ከእንግዲህ ወዲህ አይስረቅ፣ ነገር ግን በዚያ ፈንታ . . . በገዛ እጆቹ መልካምን እየሠራ ይድከም።”—ኤፌሶን 4:28

በአካልም ሆነ በሥነ ምግባር ንጹሕ ሁን። “በእግዚአብሔር ፍርሃት ቅድስናን ፍጹም እያደረግን ሥጋንና መንፈስን ከሚያረክስ ሁሉ ራሳችንን እናንጻ።”—2 ቆሮንቶስ 7:1

አንድ ቤተሰብ አብሮ ለመመገብ ምግብ ሲያቀራርብ

የቤተሰብ አባሎችህን በፍቅርና በአክብሮት ያዝ። “እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንዲህ እንደ ራሱ አድርጎ ይውደዳት፣ ሚስቱም ባልዋን ትፍራ። ልጆች ሆይ፣ ለወላጆቻችሁ በጌታ ታዘዙ።”—ኤፌሶን 5:33–6:1

ሌሎችን አፍቅር። “ፍቅር ከእግዚአብሔር ስለሆነ . . . እርስ በርሳችን እንዋደድ።”—1 ዮሐንስ 4:7

የአገሩን ሕግ አክብር። “ነፍስ ሁሉ [ለመንግሥት] ይገዛ። . . . ለሁሉ የሚገባውን አስረክቡ፤ ግብር ለሚገባው ግብርን፣ ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን።”—ሮሜ 13:1, 7

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ