የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • gf ትምህርት 16 ገጽ 26-27
  • ለአምላክ ያለህን ፍቅር አሳይ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ለአምላክ ያለህን ፍቅር አሳይ
  • የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ‘አምላክ በደስታ የሚሰጠውን ሰው ይወዳል’
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2013
  • የይሖዋ ወዳጅ መሆን ትችላለህ
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
  • አምላክ ወዳጁ እንድትሆን ይጋብዝሃል
    የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
  • ይሖዋ በደስታ የሚሰጠውን ይወዳል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1992
ለተጨማሪ መረጃ
የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
gf ትምህርት 16 ገጽ 26-27

ትምህርት 16

ለአምላክ ያለህን ፍቅር አሳይ

አንድ ሰው ሲጸልይና መጽሐፍ ቅዱስ ሲያነብ

ከጓደኛህ ጋር ያለህን ወዳጅነት ጠብቀህ ለማቆየት ከእርሱ ጋር መነጋገር ይኖርብሃል። እርሱ ሲናገር ታዳምጠዋለህ እርሱም አንተ ስትናገር ያዳምጥሃል። በተጨማሪም ስለ ወዳጅህ ጥሩ ነገሮችን ለሌሎች ትናገራለህ። ከአምላክ ጋር ወዳጅ መሆንም ከዚህ ጋር ተመሳሳይ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ ጉዳይ ምን እንደሚል መርምር:-

በጸሎት አማካኝነት ከይሖዋ ጋር ዘወትር ተነጋገር። “በጸሎት ጽ[ና]።”—ሮሜ 12:12

የአምላክ ቃል የሆነውን መጽሐፍ ቅዱስን አንብብ። “የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።”—2 ጢሞቴዎስ 3:16

ስለ አምላክ ሌሎችን አስተምር። “ሂዱና አሕዛብን ሁሉ . . . ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው።”—ማቴዎስ 28:19, 20

ሁለት የይሖዋ ምሥክሮች ለአንድ ሰው ሲሰብኩ

ከአምላክ ወዳጆች ጋር ተቀራረብ። “ከጠቢባን ጋር የሚሄድ ጠቢብ ይሆናል።”—ምሳሌ 13:20

በመንግሥት አዳራሽ በሚደረጉ ስብሰባዎች ላይ ተገኝ። “ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤ . . . እንመካከር።”—ዕብራውያን 10:24, 25

የመንግሥቱን ሥራ ደግፍ። “እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ።”—2 ቆሮንቶስ 9:7

የይሖዋ ምሥክሮች በመንግሥት አዳራሽ ውስጥ
    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ