የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • scl ገጽ 13-15
  • ልጆች፤ ወጣቶች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ልጆች፤ ወጣቶች
  • ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
scl ገጽ 13-15

ልጆች፤ ወጣቶች

አምላክ ለልጆች ያለው አመለካከት

ይሖዋ ልጆችንና ወጣቶችን ከፍ አድርጎ እንደሚመለከታቸው ያሳየው እንዴት ነው?

ዘዳ 6:6, 7፤ 14:28, 29፤ መዝ 110:3፤ 127:3-5፤ 128:3, 4፤ ያዕ 1:27

በተጨማሪም ኢዮብ 29:12፤ መዝ 27:10፤ ምሳሌ 17:6⁠ን ተመልከት

በተጨማሪም “ቤተሰብ” የሚለውን ተመልከት

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘፍ 1:27, 28—ይሖዋ ምድር በሰው ልጆች እንድትሞላ ባወጣው የመጀመሪያ ዓላማ ላይ ልጅ መውለድ ቁልፍ ሚና አለው

    • ዘፍ 9:1—ከጥፋት ውኃ በኋላ ምድር ዳግመኛ በሰዎች እንድትሞላ አምላክ የሰጠው ትእዝዝ እንዲፈጸም ልጅ መውለድ ትልቅ ድርሻ አለው

    • ዘፍ 33:5—ታማኙ ያዕቆብ፣ ልጆቹ በአምላክ ቸርነት ያገኛቸው ስጦታዎች እንደሆኑ ተሰምቶታል

    • ማር 10:13-16—ኢየሱስ እንደ አባቱ ልጆችን ይወዳል

ይሖዋ ልጆችን ስለሚበድሉ ወይም መጠቀሚያ ስለሚያደርጉ ሰዎች ምን ይሰማዋል?

ዘፀ 22:22-24፤ ዘዳ 10:17, 18፤ መዝ 10:14, 15

ትናንሽ ልጆች የትልቅ ሰውን ኃላፊነት እንዲወጡ መጠበቅ ተገቢ እንዳልሆነ የሚያሳዩት የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች የትኞቹ ናቸው?

ዘኁ 1:3፤ 1ቆሮ 13:11

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘፍ 33:12-14—ያዕቆብ ልጆቹ አቅም እንደሌላቸውና ከአዋቂ ሰው እኩል መራመድ እንደማይችሉ ተረድቶላቸዋል

ልጆች ላይ ለሚደርሰው መከራ ተጠያቂው አምላክ ነው?

ኢዮብ 34:10፤ ያዕ 1:13፤ 1ዮሐ 5:19

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ሉቃስ 5:18, 20, 23-25—ኢየሱስ የበሽታ መንስኤ ኃጢአት እንደሆነ ተናግሯል

    • ሮም 5:12—ሐዋርያው ጳውሎስ የኃጢአትና የሞት መንስኤ ምን እንደሆነ አስረድቷል

በልጆችም ሆነ በአዋቂዎች ላይ የሚደርሰው መከራ እንደሚያበቃ ይሖዋ ምን ማረጋገጫ ሰጥቷል?

ኢሳ 11:6-9፤ ዮሐ 3:16፤ ሥራ 24:15፤ ራእይ 21:4

አንድ ልጅ ጥሩ ምሳሌ የማይሆኑ ወላጆች ስላሳደጉት ወይም በልጅነቱ ስለተበደለ፣ አዋቂ ሲሆን ከሌሎች ያነሰ ይሆናል ወይም የወላጆቹን ስህተት ይደግማል ማለት ነው?

ዘዳ 24:16፤ ሕዝ 18:1-3, 14-18

በተጨማሪም ዘዳ 30:15, 16⁠ን ተመልከት

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 2ነገ 18:1-7፤ 2ዜና 28:1-4—የሕዝቅያስ አባት ልጆቹን መሥዋዕት እስከማድረግ የደረሰ ክፉ ሰው ነበር፤ ሕዝቅያስ ግን ታማኝና ግሩም ንጉሥ ሆኗል

    • 2ነገ 21:19-26፤ 22:1, 2—ኢዮስያስ፣ አባቱ አምዖን ክፉ ሰው ቢሆንም በጣም ጥሩ ንጉሥ መሆን ችሏል

    • 1ቆሮ 10:11, 12—ሐዋርያው ጳውሎስ ከሌሎች ስህተት መማርና ተመሳሳይ ስህተት ከመፈጸም መቆጠብ እንደምንችል ተናግሯል

    • ፊልጵ 2:12, 13—ሐዋርያው ጳውሎስ የራሳችንን መዳን መፈጸም በዋነኝነት የእኛ ኃላፊነት እንደሆነ ተናግሯል

ልጆችና ወጣቶች ያሉባቸው ኃላፊነቶች

ይሖዋ ፈሪሃ አምላክ ካላቸው ወላጆቻቸው ጋር ለሚኖሩ ልጆች ምን አመለካከት አለው?

1ቆሮ 7:14

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘፍ 19:12, 15—የሎጥ ልጆች የመላእክትን ጥበቃ ማግኘት የቻሉበት አንዱ ምክንያት አባታቸው ጻድቅ መሆኑ ነው

ልጆች አምላክን የሚፈሩ ወላጆች ስላሳደጓቸው ብቻ ያለምንም ጥረት በአምላክ ፊት ጥሩ አቋም እንደሚኖራቸው ሊጠብቁ ይገባል?

ምሳሌ 20:11፤ ሕዝ 18:5, 10-13

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘሌ 10:1-3, 8, 9—የሊቀ ካህናቱ አሮን ልጆች በስካር ምክንያት ሳይሆን አይቀርም ተቀስፈዋል

    • 1ሳሙ 8:1-5—ሳሙኤል ጻድቅ ነቢይ ቢሆንም ልጆቹ ምግባረ ብልሹ ነበሩ

ልጆች የአምላክን ሞገስ ማግኘት ከፈለጉ ምን ማድረግ አለባቸው?

ምሳሌ 1:8፤ 27:11፤ ኤፌ 6:1-3

ልጆች በጉባኤ ስብሰባዎች ላይ መገኘት ያለባቸው ለምንድን ነው?

ዘዳ 31:12, 13፤ ዕብ 10:24, 25

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ማቴ 15:32-38—ከኢየሱስ አድማጮች መካከል ትናንሽ ልጆችም ይገኙበታል

ይሖዋ ልጆች እንዲያገለግሉት እንደሚፈልግ በምን እናውቃለን?

መዝ 8:2፤ 148:12, 13

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 1ሳሙ 17:4, 8-10, 41, 42, 45-51—ወጣቱ ዳዊት፣ አንድን ግዙፍና ጨካኝ ሰው ድል በማድረግ ስሙን እንዲያስከብር ይሖዋ ተጠቅሞበታል

    • 2ነገ 5:1-15—ይሖዋ በአንዲት ትንሽ እስራኤላዊት ልጅ በመጠቀም እስራኤላዊ ያልሆነን የሠራዊት አለቃ ስለ እውነተኛው አምላክ እንዲማር ረድቶታል

    • ማቴ 21:15, 16—ኢየሱስ፣ ልጆች መሲሑን ለማወደስ ያደረጉትን ጥረት አድንቋል

ይሖዋ የማያምኑ ወላጆች ላሏቸው ልጆች ምን አመለካከት አለው?

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘኁ 16:25, 26, 32, 33—ይሖዋ በነቢዩ ሙሴና በሊቀ ካህናቱ አሮን ላይ ባመፁት ሰዎች ላይ የወሰደው የፍርድ እርምጃ ቤተሰቦቻቸውንም ነክቷል

    • ዘኁ 26:10, 11—ዓመፀኛው ቆሬ በሞት ቢቀጣም ልጆቹ ለአምላክ ታማኝ በመሆናቸው ከጥፋት ተርፈዋል

በዛሬው ጊዜ ያሉ ወጣቶች ጓደኞቻቸውን በጥበብ መምረጥ ያለባቸው ለምንድን ነው?

ምሳሌ 13:20፤ 1ቆሮ 15:33

በተጨማሪም 2ጢሞ 3:1-5⁠ን ተመልከት

ክርስቲያን ወጣቶች ምን ዓይነት ጓደኞችን መምረጥ አለባቸው?

2ጢሞ 2:22

በተጨማሪም “ወዳጅነት” የሚለውን ተመልከት

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ