የርዕስ ማውጫ
ከየካቲት 27, 2017–መጋቢት 5, 2017 ባለው ሳምንት
7 “በይሖዋ ታመን፤ መልካም የሆነውንም አድርግ”
ይህ የጥናት ርዕስ፣ የ2017 የዓመት ጥቅሳችን ተፈታታኝ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙን የይሖዋን እርዳታ እንድንፈልግ የሚያበረታታን እንዴት እንደሆነ ያብራራል። በጥንት ዘመን የኖሩ ታማኝ የይሖዋ አገልጋዮች የተዉትን ምሳሌ በመከተል፣ ችግሮች ሲያጋጥሙን በይሖዋ እንደምንታመን ማሳየት በሌላ በኩል ደግሞ እጃችንን አጣጥፈን ከመቀመጥ ይልቅ ለችግሮቻችን መፍትሔ መፈለግም ሆነ ሌሎችን መርዳት የምንችለው እንዴት እንደሆነ እንመለከታለን።
ከመጋቢት 6-12, 2017 ባለው ሳምንት
በዚህ የጥናት ርዕስ ላይ የመምረጥ ነፃነታችንን ይህን ስጦታ የሰጠንን አካል በሚያስደስት መልኩ በመጠቀም ለዚህ ስጦታ አድናቆት እንዳለን ማሳየት የምንችለው እንዴት እንደሆነ እንማራለን። በተጨማሪም የሌሎችን የመምረጥ ነፃነት እንደምናከብር ማሳየት የምንችለው እንዴት እንደሆነ እንመለከታለን።
ከመጋቢት 13-19, 2017 ባለው ሳምንት
17 ልክን ማወቅ ዛሬም አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
ከመጋቢት 20-26, 2017 ባለው ሳምንት
22 ተፈታታኝ ሁኔታ በሚያጋጥመን ጊዜም ልካችንን ማወቅ
እነዚህ ሁለት የጥናት ርዕሶች አስፈላጊ ስለሆነው ባሕርይ ማለትም ልክን ስለማወቅ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረን ይረዱናል። የመጀመሪያው የጥናት ርዕስ ‘ልክን ማወቅ ሲባል ምን ማለት ነው? ምን ማለትስ አይደለም?’ ለሚሉት ጥያቄዎች መልስ ይሰጣል። ሁለተኛው የጥናት ርዕስ ደግሞ ተፈታታኝ ሁኔታዎች በሚያጋጥሙን ጊዜም እንኳ ይህን ባሕርይ ማሳየት የምንችለው እንዴት እንደሆነ ያብራራል።
ከመጋቢት 27, 2017–ሚያዝያ 2, 2017 ባለው ሳምንት
27 እነዚህን ነገሮች “ታማኝ ለሆኑ ሰዎች አደራ ስጥ”
አንድ ትውልድ አልፎ ሌላ ትውልድ ሲተካ በዕድሜ የገፉ ወንድሞች ያከናውኑ የነበሩትን ሥራ ወጣቶች ተረክበው መሥራት ይጀምራሉ። ይህ የጥናት ርዕስ፣ በዕድሜ የገፉም ሆኑ ወጣቶች ለዚህ ለውጥ ትክክለኛ አመለካከት ማዳበር የሚችሉት እንዴት እንደሆነ ያብራራል።
32 ይህን ያውቁ ኖሯል?