ማስታወቂያዎች
◼ የምንጠቀምባቸው ጽሑፎች በግንቦት፦ መጠበቂያ ግንብና ንቁ! መጽሔቶች እንዲሁም ኮንትራት ማስገባት። በተደጋጋሚ በተሸፈኑ ክልሎች (ትምህርት ቤትና የይሖዋ ምሥክሮች ከተባለው ብሮሹር በስተቀር) ማንኛውንም ብሮሹር መጠቀም ይቻላል። ሰኔ፦ ቤተሰብ እና/ወይም ወጣትነትህ የተባሉት መጻሕፍት በ3 ብር ይበረከታሉ። ሐምሌ እና ነሐሴ፦ ከሚከተሉት ውስጥ ማንኛውንም ባለ 32 ገጽ ብሮሹር መጠቀም ይቻላል:- አምላክ ስለ እኛ በእርግጥ ያስባልን?፣ በምድር ላይ ለዘላለም በደስታ ኑር!፣ “እነሆ፣ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ” (እንግሊዝኛ)፣ በሥላሴ ማመን ይገባሃልን?፣ ለዘላለም ጸንቶ የሚኖረው መለኮታዊው ስም (እንግሊዝኛ)፣ የአምላክ መንግሥት ገነትን ታመጣለች፣ የሕይወት ዓላማ ምንድን ነው? (እንግሊዝኛ) እና የምትወዱት ሰው ሲሞት (እንግሊዝኛ)። ማሳሰቢያ፦ ከላይ የተጠቀሱትን የዘመቻ ጽሑፎች እስካሁን ያልጠየቁ ጉባኤዎች በቀጣዩ ወር የጽሑፍ ማዘዣ ቅጽ (S–14–AM) መጠየቅ አለባቸው።
◼ ጽሑፍ ለመውሰድም ሆነ ገንዘብ ለመክፈል ወደ ቤቴል የምትመጡ ሁሉ በሳምንቱ ውስጥ ሰኞና ሐሙስ ብቻ ለዚሁ የተወሰኑ መሆናቸውን እናስታውቃለን። ከአዲስ አበባ ውጭ የምትመጡ ወንድሞችም በተቻለ መጠን በእነዚሁ ቀናት ለመስተናገድ እንድትሞክሩና አስቸኳይ ሁኔታ ካጋጠማችሁ ግን እንደምናስተናግዳችሁ እንገልጻለን።
◼ የአውራጃ ስብሰባ፦ በማስታወቂያ በአዋሳ ይደረጋል ተብሎ የተነገረው የአውራጃ ስብሰባ ቀርቶ በዚያው ጊዜ ከመስከረም 15–17, 1995 በሻሸመኔ ከተማ ይደረጋል።