ማስታወቂያዎች
◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች:- ኅዳር፦ የመንግሥት ዜና ቁ. 35ን ማሰራጨታችንን እንቀጥላለን። በእያንዳንዱ ቤት ወይም መኖሪያ ላሉ ሰዎች የመንግሥት ዜና ቁ. 35ን ቅጂ በማዳረስ ክልላቸውን የሸፈኑ ጉባኤዎች እውቀት የተባለውን መጽሐፍ ማበርከት ይችላሉ። ታኅሣሥ፦ ታላቁ ሰው (የእንግሊዝኛ) ወይም የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ።
◼ ኅዳር 16 ልዩ ዘመቻው ከተጠናቀቀ በኋላ የመንግሥት ዜና ቁ. 35 በእጃቸው ያለ ጉባኤዎች ሌሎች ትራክቶች በሚበረከቱበት መንገድ ከቤት ወደ ቤትም ሆነ በሌላ ቦታ አስፋፊዎች እንዲጠቀሙባቸው ማበረታታት ይችላሉ። አስፋፊዎች አመቺ ሆኖ ካገኙት ቤት ባልተገኙት ሰዎች ደጃፍ አንድ ትራክት ትተው መሄድ ይችላሉ። ይህንንም ሲያደርጉ በዚያ የሚያልፉ ሰዎች የማያዩበት ቦታ ማስቀመጥ አለባቸው። የዚህን አስፈላጊ መልእክት ቀሪ ቅጂዎች ሁሉ ለማሰራጨት ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል።
◼ ጉባኤዎች በኅዳር ወር በሚልኩት የጽሑፍ ማዘዣ ላይ የ1998 የይሖዋ ምስክሮች የዓመት መጽሐፍ ማዘዝ መጀመር ይኖርባቸዋል።
◼ ከመጋቢት እስከ ግንቦት 1998 በሚደረገው የአገልግሎት ዘመቻ ወቅት ጊዜያዊ ልዩ አቅኚ ለመሆን የምትፈልጉ የዘወትር አቅኚዎች በጉባኤያችሁ የአገልግሎት ኮሚቴ በኩል ልታመለክቱ ትችላላችሁ። ኮሚቴውም ድጋፍ የሰጠባቸውን ማመልከቻዎች እስከ ታኅሣሥ 31, 1997 ድረስ እንዲልክልን እንጠይቃለን።
◼ አዲስ የወጣ የቪዲዮ ካሴት:-
ኖአ—ሂ ዎክድ ዊዝ ጎድ—እንግሊዝኛ