ማስታወቂያዎች
◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች:- ከመስከረም እስከ ታኅሣሥ፦ በምድር ላይ በገነት ለዘላለም መኖር ትችላለህ በ3.00 ብር።
◼ በመስከረም 1 ወይም ከዚያ ብዙ ሳይቆይ ሰብሳቢ የበላይ ተመልካቹ ወይም እሱ የወከለው ሰው የጉባኤውን ሒሳብ መመርመር ይኖርበታል። ሒሳቡ ከተመረመረ በኋላ ውጤቱን ለጉባኤው አስታውቁ።
◼ ሽማግሌዎች የመመለስ ዝንባሌ ያላቸውን የተወገዱ ወይም ራሳቸውን ያገለሉ ግለሰቦች በተመለከተ በሚያዝያ 15, 1991 መጠበቂያ ግንብ ከገጽ 21-3 ላይ የተሰጡትን መመሪያዎች እንዲሠሩባቸው ልናሳስባቸው እንወዳለን።
◼ ጉባኤ የሚሰበሰቡ ሁሉ የግል ኮንትራታቸውን ጨምሮ የመጠበቂያ ግንብ እና የንቁ! መጽሔቶች ኮንትራት ሲያስገቡም ሆነ ሲያሳድሱ መላክ ያለባቸው በጉባኤ በኩል ነው።
◼ አስፋፊዎች በግል የሚልኩትን የጽሑፍ ትእዛዝ ማኅበሩ አያስተናግድም። የጉባኤው ወርኃዊ የጽሑፍ ትእዛዝ ወደ ማኅበሩ ከመላኩ በፊት በግል የሚታዘዙ ነገሮች ማግኘት የሚፈልጉ ሁሉ ለጽሑፍ አገልጋዩ ማስታወቅ እንዲችሉ ሰብሳቢ የበላይ ተመልካቹ በየወሩ ማስታወቂያ እንዲነገር ዝግጅት ማድረግ ይኖርበታል። በልዩ ትእዛዝ የሚገኙት የትኞቹ ጽሑፎች እንደሆኑ እባካችሁ አስታውሱ።
◼ በእጃችን የሚገኝ አዲስ ጽሑፍ:- የ1998 የይሖዋ ምሥክሮች የዓመት መጽሐፍ።