የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 4/04 ገጽ 1
  • ወጣቶች—የአምላክን ቃል አንብቡ!

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ወጣቶች—የአምላክን ቃል አንብቡ!
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2004
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ውሳኔ የምታደርጉት እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
  • እናንት ወጣቶች፣ ትኩረታችሁ ያረፈው በመንፈሳዊ ግቦች ላይ ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
  • ወጣቶች ሆይ፣ የይሖዋን ልብ አስደስቱ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1993
  • እምነት በማዳበር ጥበብ የሚንጸባረቅበት ውሳኔ አድርጉ!
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2004
km 4/04 ገጽ 1

ወጣቶች​—⁠የአምላክን ቃል አንብቡ!

1 ወጣትነት ፈተናዎች የሚያጋጥሙበትና ከባድ ውሳኔዎች የሚደረጉበት ወቅት ነው። ብዙ ወጣት ክርስቲያኖች በየዕለቱ የአምላክን የሥነ ምግባር መስፈርቶች እንዲጥሱ ተጽዕኖዎች ይደረጉባቸዋል። ከትምህርት፣ ከሥራና ከጋብቻ ጋር በተያያዘ ማንኛውንም ውሳኔ ከማድረጋችሁ በፊት መንፈሳዊ ግቦችን ማውጣት ይኖርባችኋል። ሌሎች ውሳኔዎቻችሁ በቀሪው ሕይወታችሁ ላይ በጎ ተጽዕኖ እንዲኖራቸው ማድረግ የምትችሉት በዚህ መንገድ ብቻ ነው። በግልጽ የተቀመጡ መንፈሳዊ ግቦች ያሏችሁ መሆኑ በማስተዋል እርምጃ እንድትወስዱና መንገዳችሁ የተቃና እንዲሆን ይረዳችኋል። የአምላክን ቃል ዘወትር የምታነብቡና የምታሰላስሉ ከሆነ በመንፈስ አነሳሽነት ከተጻፈው ምክሩ ጋር ተስማምታችሁ እንድትኖሩ የሚገፋፋችሁ ከመሆኑም በላይ የምታደርጓቸው መልካም ጥረቶች ይሳኩላችኋል።​—⁠ኢያሱ 1:8፤ መዝ. 1:2, 3

2 መጽሐፍ ቅዱስን ማንበባችሁ የሚጠቅማችሁ እንዴት ነው? የሰይጣን ዓለም መጥፎ ድርጊቶችን እንድንፈጽም በሚገፋፉ ማባበያዎች የተሞላ ነው። (1 ዮሐ. 2:15, 16) እናንተም ከክፍላችሁ ተማሪዎች ወይም በእናንተ ዕድሜ ካሉ ልጆች መካከል በእኩዮቻቸው ግፊት በመሸነፋቸው ምክንያት ለችግር የተዳረጉ ወጣቶችን ታውቁ ይሆናል። የመጽሐፍ ቅዱስን ምክር በጥብቅ መከተላችሁ ኃጢአት ከመሥራት እንድትቆጠቡ የሚያስችል ሥነ ምግባራዊና መንፈሳዊ ጥንካሬ ይሰጣችኋል። ከዚህም በላይ በአምላክ ቃል ውስጥ የሚገኘው ምክር በሰይጣን ስውር ወጥመድ እንዳትያዙ ሊረዳችሁ ይችላል። (2 ቆ⁠ሮ. 2:11፤ ዕብ. 5:14) በአምላክ መንገድ መሄድ እውነተኛ ደስታ እንድታገኙ ወይም እርካታ ያለው ሕይወት እንድትመሩ ያስችላችኋል።​—⁠መዝ. 119:1, 9, 11

3 በአምላክ ቃል ውስጥ የሚገኙት ጊዜ የማይሽራቸው መሠረታዊ ሥርዓቶች ከሰብዓዊ ጥበብ እጅግ የላቁ ናቸው። (መዝ. 119:98-100) የመጽሐፍ ቅዱስን መሠረታዊ ሥርዓቶች በሚገባ ማወቃችሁና በይሖዋ ዓላማዎች ላይ ማሰላሰላችሁ እንዲሁም ልባዊ ጸሎት ማቅረባችሁ በጥበቡ አቻ ከሌለው የመጽሐፍ ቅዱስ ደራሲ ከሆነው ከይሖዋ አምላክ ጋር የቀረበ ወዳጅነት እንድትመሠርቱ ሊረዳችሁ ይችላል። እርሱ “አስተምርሃለሁ፤ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ እመክርሃለሁ፤ በዐይኔም እከታተልሃለሁ” በማለት ቃል ገብቷል።​—⁠መዝ. 32:8

4 ለማንበብ ጊዜ መድቡ:- አንዲት ወጣት ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን ከዳር እስከ ዳር ለማንበብ ግብ ያወጣች ሲሆን በአንድ ዓመት ውስጥ አንብባ ጨረሰች። ምን ጥቅም አገኘች? እንዲህ ትላለች:- “ስለ ይሖዋ ብዙ ነገሮችን ተምሬያለሁ። እነዚህ ነገሮች ወደ እርሱ ይበልጥ እንድቀርብ እንዲሁም በቀሪው ሕይወቴ እርሱን እንድፈራ የሚያደርጉ ናቸው።” (ያዕ. 4:8) እናንተስ መጽሐፍ ቅዱስን አንብባችሁ ጨርሳችኋል? ካልሆነ ለምን ግብ አታወጡም? ይሖዋ ጥረታችሁን የሚባርክ ከመሆኑም በላይ ታላላቅ በረከቶችን ታጭዳላችሁ።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ