የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 5/08 ገጽ 1
  • “ቀንበሬን ተሸከሙ”

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • “ቀንበሬን ተሸከሙ”
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2008
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • “ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነው”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1995
  • ኢየሱስ የእረፍት ምንጭ ነበር
    ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2018
  • “ወደ እኔ ኑ፤ እኔም እረፍት እሰጣችኋለሁ”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2019
  • መንፈሳዊ ነገሮች ላይ በማተኮር እረፍት አግኙ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2010
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2008
km 5/08 ገጽ 1

“ቀንበሬን ተሸከሙ”

1 ዓለማችን በውጥረትና በጭንቀት የተሞላ ቢሆንም ኢየሱስ፣ ቀንበሩን በመሸከም ለነፍሳችን እረፍት እንድናገኝ ያቀረበውን ፍቅራዊ ግብዣ መቀበላችን እፎይታ አስገኝቶልናል። (ማቴ. 11:29, 30) የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የመሆንን ቀንበር መሸከም ተፈታታኝ ሆኖም እረፍት በሚሰጥ አንድ ሥራ መካፈልን ይጨምራል። ይህ ሥራ ደግሞ የመንግሥቱን ምሥራች መስበክንና ሰዎች የኢየሱስን ልዝብ ቀንበር በመሸከም እንደኛው ለነፍሳቸው እረፍት እንዲያገኙ መርዳትን ያካትታል።—ማቴ. 24:14፤ 28:19, 20

2 አገልግሎት የሚያስገኘው እረፍት:- ኢየሱስ፣ ተከታዮቹ ከራሳቸው ሸክም በተጨማሪ የእሱን ሸክም እንዲሸከሙ አልጠየቀም። ከዚህ ይልቅ የራሳቸውን ከባድ ሸክም አውርደው የእሱን ቀላል ሸክም እንዲሸከሙ ጋብዟቸዋል። በመሆኑም ይህ ሥርዓት በሚያመጣቸው አስጨናቂና ተስፋ አስቆራጭ በሆኑ ነገሮች ልባችን እንዲዝል ማድረግም ሆነ አስተማማኝነት የሌለውን ሀብት ለማግኘት መድከም አይኖርብንም። (ሉቃስ 21:34፤ 1 ጢሞ. 6:17) ምንም እንኳ በሥራ የተወጠርን ብንሆንና የዕለት ጉርሳችንን ለማግኘት መሯሯጣችን የግድ ቢሆንም እንኳ በሕይወታችን ውስጥ ቅድሚያ የምንሰጠው ለይሖዋ አምልኮ ነው። (ማቴ. 6:33) ይበልጥ አስፈላጊ ለሆነው ነገር ትክክለኛ አመለካከት ካዳበርን ምንጊዜም ቢሆን አገልግሎት ሸክም ሳይሆን እረፍት የሚሰጥ ይሆንልናል።—ፊልጵ. 1:10

3 አብዛኛውን ጊዜ በሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ቦታ ስለምንሰጣቸው ነገሮች ማውራት ያስደስተናል። (ሉቃስ 6:45) በሁሉም ክርስቲያኖች ሕይወት ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚይዙት ደግሞ ይሖዋ እና እሱ ተስፋ የገባቸው የመንግሥቱ በረከቶች ናቸው። በመሆኑም አገልግሎት ላይ ስንሆን የዕለት ተዕለት ጭንቀታችንን ትተን ወደፊት የተሻለ ነገር እንደሚመጣ “የምሥራች” መናገራችን በእርግጥም እረፍት የሚሰጥ ነው! (ሮሜ 10:15) በአንድ ሥራ ላይ ይበልጥ ስንቆይ ብቃታችንም ሆነ የምናገኘው ደስታ የዚያኑ ያህል ይጨምራል። በመሆኑም በተቻለ መጠን ጊዜያችንን ይበልጥ በአገልግሎት የምናሳልፍ ከሆነ የምናገኘው እርካታም የዚያኑ ያህል ይጨምራል። አንዳንድ ሰዎች ለስብከቱ ሥራችን ምላሽ ሲሰጡ ማየት ምንኛ የሚያበረታታ ነው! (ሥራ 15:3) ይሖዋ በጥረታችን እንደሚደሰትና በጎ ውጤት ሁሉ የሚገኘው ከእሱ እንደሆነ ዘወትር የምናስታውስ ከሆነ፣ አገልግሎታችን ግድየለሽ ወይም ተቃዋሚ ሰዎች ቢያጋጥሙንም እንኳ መንፈስን የሚያድስ ይሆንልናል።—ሥራ 5:41፤ 1 ቆሮ. 3:9

4 የኢየሱስን ግብዣ የምንቀበል ከሆነ የይሖዋ ምሥክሮች በመሆን ከእሱ ጋር አብረን የማገልገል መብት ይኖረናል። (ኢሳ. 43:10፤ ራእይ 1:5) ከዚህ የበለጠ እረፍት የሚሰጥ ምን ነገር ይኖራል?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ