የመስክ አገልግሎት ጎላ ያሉ ገጽታዎች
ሰዎች በመታሰቢያው በዓል ላይ እንዲገኙ ለመጋበዝ በአገራችን በሚነገሩ በአምስት ቋንቋዎች የተዘጋጀውን ማራኪ የሆነ የመጋበዣ ወረቀት ለማሰራጨት ልዩ ጥረት እንዳደረግን የታወቀ ነው፤ እስካሁን የደረሰን አኃዝ የተሟላ ባይሆንም 24,701 ሰዎች በበዓሉ ላይ እንደተገኙ ሪፖርት ተደርጓል። በመሆኑም ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ የተሰብሳቢዎች ቁጥር አግኝተናል። ይህ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው በዓል ቢያንስ በአሥር አዳዲስ ክልሎች ለመጀመሪያ ጊዜ ተከብሯል። ለምሳሌ፣ ስድስት አስፋፊዎች በሚገኙበት በአንድ ገጠራማ ክልል 149 ሰዎች በበዓሉ ላይ ተገኝተዋል! እንግዲያው ሁላችንም እነዚህ በበዓሉ ላይ የተገኙትን ፍላጎት ያሳዩ ሰዎች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እንዲጀምሩ የምናደርገውን ጥረት እንቀጥል!
በሚያዝያ ወር፣ አጠቃላይ የመስክ አገልግሎት እንቅስቃሴያችንም ከፍተኛ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን ይህም ለይሖዋ ታላቅ ውዳሴ አምጥቷል። በዚህ ወርም 8,612 አዲስ ከፍተኛ የአስፋፊዎች ቁጥር ሪፖርት እንደተደረገ መስማታችን አስደስቶናል። በዚህ ወር 1,122 ረዳት አቅኚዎች የነበሩን ሲሆን ይህም በመጋቢት ወር ሪፖርት ከተደረገው ቁጥር ይበልጣል፤ ከጠቅላላው አስፋፊዎች መካከል ወደ 30 በመቶ የሚሆኑት በአንድ ዓይነት የሙሉ ጊዜ አገልግሎት ዘርፍ ተካፍለዋል!