ጥቅምት 19 የሚጀምር ሳምንት
ጥቅምት 19 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 39 (86)
❑ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
lv ምዕ. 4 ከገጽ 46 እስከ 49 ያሉት ሣጥኖች
❑ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ዘዳግም 7-10
ቁ. 1፦ ዘዳግም 9:1-14
ቁ. 2፦ ኢየሱስን መውደድ ያለብን ለምንድን ነው? (lr ምዕ. 38)
ቁ. 3፦ መጽሐፍ ቅዱስ ስንት ሰዎች የሰማያዊ ሕይወት ተስፋ እንዳላቸው ያሳያል? (rs ገጽ 166 አን. 4-5)
❑ የአገልግሎት ስብሰባ፦
መዝሙር 49 (114)
5 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች።
15 ደቂቃ፦ ምርምር ማድረግ ግንዛቤ ያሰፋል። በአገልግሎት ትምህርት ቤት መጽሐፍ ከገጽ 33 እስከ ገጽ 34 ላይ እስከሚገኘው ንዑስ ርዕስ ድረስ ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ የሚቀርብ ንግግር። ይህ ንግግር አስፋፊዎች ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶቻቸው ምርምር ማድረግ የሚቻልበትን መንገድ እንዲያሳዩአቸው በሚያበረታታ መንገድ መቅረብ አለበት፤ ጥናቶች እንዲህ ያለውን ምርምር ማድረጋቸው እምነታቸው እንዲጠናከርና ለሌሎች መመሥከር እንዲችሉ ይረዳቸዋል። አንድ አስፋፊ ጥናቱ ምርምር የማድረግን አስፈላጊነት እንዲገነዘብ ሊረዳው የሚችለው እንዴት እንደሆነ የሚያሳይ አንድ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
15 ደቂቃ፦ “በስልክ የሚሰጥ ምሥክርነት ውጤታማ ሊሆን ይችላል።” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። ሁለት አስፋፊዎች በዚህ ወር የሚበረከተውን ጽሑፍ ተጠቅመው በስልክ ሲመሠክሩ የሚያሳዩ ሁለት ሠርቶ ማሳያዎች እንዲያቀርቡ አድርግ። ማሳሰቢያ፦ በአገሪቱ ውስጥ በስልክ ከመመሥከር ጋር በተያያዘ የወጣ ሕግ ካለ እንዲህ ያለው ሕግ ግምት ውስጥ መግባት ይኖርበታል።
መዝሙር 57 (136)