ግንቦት 30 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ግንቦት 30 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 33 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
dp ምዕ. 13 አን. 1-11 (25 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ መዝሙር 26-33 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ መዝሙር 31:9-24 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ እውነተኛ ትሕትና በማሳየት ረገድ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እነማን ምሳሌ ይሆኑናል? (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ አይሁዳውያን ለመዳን በኢየሱስ ማመን ይኖርባቸዋል?—rs ከገጽ 223 አን. 4 እስከ ገጽ 224 አን. 1 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች። በቅርብ ጊዜ ለደረሰን መጠበቂያ ግንብ የተዘጋጀውን የናሙና አቀራረብ በመጠቀም በሰኔ ወር የመጀመሪያ ቅዳሜ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እንዴት ማስጀመር እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ። ሁሉም ጥናት ለማስጀመር ጥረት እንዲያደርጉ አበረታታ።
15 ደቂቃ፦ ምርምር ማድረግ የሚቻለው እንዴት ነው? በአገልግሎት ትምህርት ቤት መጽሐፍ ከገጽ 33-38 ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። አንድ አስፋፊ በአገልግሎት ላይ ለቀረበለት ጥያቄ መልስ ለማግኘት በጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ሲያደርግ የሚያሳይ አጠር ያለ መነባንብ እንዲቀርብ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ በሰኔ ወር መጽሔቶችን ለማበርከት ዝግጅት አድርጉ። በውይይት የሚቀርብ። በአንድ ወይም በሁለት ደቂቃዎች ውስጥ የመጽሔቶቹን ይዘት ተናገር። ከዚያም ሁለት ወይም ሦስት ርዕሶችን ምረጥና መጽሔቶቹን ለማስተዋወቅ ምን ጥያቄ ማንሳት እንዲሁም የትኛውን ጥቅስ ማንበብ እንደሚቻል አድማጮችን ጠይቅ። እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
መዝሙር 37 እና ጸሎት