ሰኔ 27 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ሰኔ 27 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 37 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
dp ምዕ. 14 አን. 1-9 (25 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ መዝሙር 52-59 (10 ደቂቃ)
የቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ክለሳ (20 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች። “መያዝ ያለብኝ ምን ያህል ሰዓት ነው?” በሽማግሌ የሚቀርብ ንግግር። ከንግግሩ በኋላ በገጽ 4 ላይ የሚገኘውን የአቀራረብ ናሙና በመጠቀም በሐምሌ ወር የመጀመሪያው ቅዳሜ እንዴት ጥናት ማስጀመር እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ። በዚህ ዕለት ሁሉም ተሳትፎ እንዲያደርጉ አበረታታ።
10 ደቂቃ፦ በሐምሌ ወር መጽሔቶችን ለማበርከት ዝግጅት አድርጉ። በውይይት የሚቀርብ። በአንድ ወይም በሁለት ደቂቃ ውስጥ የመጽሔቶቹን ይዘት ተናገር። ከዚያም ሁለት ወይም ሦስት ርዕሶችን ምረጥና እነዚህን ርዕሶች ለማስተዋወቅ ምን ጥያቄ ማንሳት እንዲሁም የትኛውን ጥቅስ ማንበብ እንደሚቻል አድማጮችን ጠይቅ። እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
15 ደቂቃ፦ በምንሰብክበት ወቅት በአነጋገራችን ዘዴኛ መሆን። በአገልግሎት ትምህርት ቤት መጽሐፍ ከገጽ 197 እስከ 199 አንቀጽ 4 ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። አንድ አስፋፊ በአካባቢያችሁ ለተለመደ አንድ የተቃውሞ ሐሳብ ዘዴ በጎደለው መንገድ ምላሽ ሲሰጥ የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ። ከዚያም አስፋፊው ያንኑ የተቃውሞ ሐሳብ ዘዴ በታከለበት መንገድ መልስ ሲሰጥ የሚያሳይ ሌላ ሠርቶ ማሳያ እንዲያቀርብ አድርግ።
መዝሙር 47 እና ጸሎት