የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 11/11 ገጽ 3
  • የጥሩ አስተማሪ መለያ ባሕርይ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የጥሩ አስተማሪ መለያ ባሕርይ
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በፍቅር በማስተማር ኢየሱስን ምሰሉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
  • ፍቅር—ውድ የሆነ ባሕርይ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
  • በፍቅር ታነጹ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
  • ፈጽሞ የማይከስመውን ፍቅርን አዳብሩ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
km 11/11 ገጽ 3

የጥሩ አስተማሪ መለያ ባሕርይ

1. የጥሩ አስተማሪ መለያ ባሕርይ ምንድን ነው?

1 አንድን ሰው ጥሩ አስተማሪ እንዲሆን የሚያስችለው ነገር ምንድን ነው? ዓለማዊ ትምህርት፣ ግለሰቡ ያካበተው ተሞክሮ ነው ወይስ ያለው የተፈጥሮ ችሎታ? አንድን ሰው ጥሩ አስተማሪ የሚያደርገው ፍቅር ነው። ፍቅር የሕጉ ማጠቃለያ ሲሆን የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ተለይተው የሚታወቁትም በዚህ ባሕርይ ነው፤ ከዚህም በተጨማሪ ይሖዋ ካሉት ዋና ዋና ባሕርያት መካከል ጎልቶ የሚጠቀሰውና ማራኪ የሆነው ይህ ባሕርይ ነው። (ዮሐ. 13:35፤ ገላ. 5:14፤ 1 ዮሐ. 4:8) ጥሩ አስተማሪዎች ፍቅርን ያንጸባርቃሉ።

2. ለሰዎች ፍቅር ማሳየታችን አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

2 ሰዎችን ውደዱ፦ ታላቅ አስተማሪ የሆነው ኢየሱስ ለሰዎች ፍቅር አሳይቷል፤ እንዲህ ማድረጉ ሰዎች እንዲያዳምጡት አነሳስቷቸዋል። (ሉቃስ 5:12, 13፤ ዮሐ. 13:1፤ 15:13) ለሰዎች የምናስብ ከሆነ ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ እንመሠክራለን። ስደትም ሆነ የሰዎች ግድየለሽነት ከመስበክ ወደኋላ እንድንል አያደርገንም። ለምንሰብክላቸው ሰዎች ከልብ የመነጨ አሳቢነት የምናሳይ ከመሆኑም ሌላ ሁኔታቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት አቀራረባችንን እንቀያይራለን። እያንዳንዱን ጥናት ለመምራት ብቻ ሳይሆን ከእያንዳንዱ ጥናት በፊት ለመዘጋጀትም ጊዜ እንመድባለን።

3. ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች ያለን ፍቅር ለአገልግሎታችን የሚጠቅመን እንዴት ነው?

3 የመጽሐፍ ቅዱስን እውነቶች ውደዱ፦ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስን እውነቶች ይወድ የነበረ ሲሆን እነዚህን እውነቶች እንደከበረ ሀብት ይመለከታቸው ነበር። (ማቴ. 13:52) እውነትን የምንወድ ከሆነ ከልብ በመነጨ ስሜት ስለምንናገር ሰዎች በጉጉት ያዳምጡናል። የዚህ ዓይነቱ ፍቅር ድክመቶቻችን ላይ ከማተኮር ይልቅ ለሰዎች በምንሰብከው ውድ የሆነ መልእክት ላይ እንድናተኩር ያደርገናል፤ ይህ ደግሞ በአገልግሎት ላይ ስንሆን የሚሰማንን ፍርሃት ይቀንስልናል።

4. ፍቅርን ማዳበር የምንችለው እንዴት ነው?

4 ፍቅርን አዳብሩ፦ ለሰዎች ፍቅር ማዳበር የምንችለው እንዴት ነው? ይሖዋና ልጁ ባሳዩን ፍቅር ላይ በማሰላሰል እንዲሁም በክልላችን ያሉ ሰዎች አሳዛኝ በሆነ መንፈሳዊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ በማሰብ ነው። (ማር. 6:34፤ 1 ዮሐ. 4:10, 11) አዘውትረን የግል ጥናት ማድረጋችንና ማሰላሰላችን ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች ያለን ፍቅር እንዲያድግ ይረዳናል። ፍቅር ከመንፈስ ፍሬ ገጽታዎች መካከል አንዱ ነው። (ገላ. 5:22) በመሆኑም ይሖዋ መንፈስ ቅዱስን እንዲሰጠን እንዲሁም ፍቅርን ማዳበር እንድንችል እንዲረዳን መለመን እንችላለን። (ሉቃስ 11:13፤ 1 ዮሐ. 5:14) ስለዚህ የትምህርት ደረጃችን፣ በእውነት ቤት ያሳለፍነው ተሞክሮ እንዲሁም የተፈጥሮ ችሎታችን ምንም ይሁን ምን ፍቅርን በማንጸባረቅ ውጤታማ አስተማሪዎች መሆን እንችላለን።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ