ግንቦት 20 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ግንቦት 20 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 42 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
cf ምዕ. 6 ከአን. 1-9 (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ዮሐንስ 8-11 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ዮሐንስ 8:12-30 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ሐሰተኛ አስተማሪዎች እንዳያታልሉን ራሳችንን ለመጠበቅ ምን እርምጃዎች መውሰድ እንችላለን?—ሮም 16:17፤ 2 ዮሐ. 9-11 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ አምላክ ‘እኔን የሚታዘዙ ሰዎች ሁሉ ለዘላለም እንዲኖሩ ፈቅጃለሁ’ ብሎ ለምን አይናገርም ነበር?—rs ገጽ 307 አን. 1-4 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ አገልግሎትህን ማስፋት የምትችልባቸው መንገዶች—ክፍል 3። የተደራጀ ሕዝብ በተባለው መጽሐፍ ከገጽ 116 አንቀጽ 1 እስከ ገጽ 117 አንቀጽ 1 ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ።
10 ደቂቃ፦ ይሖዋ ኃላፊነታችንን እንድንወጣ ይረዳናል። (ዘፀ. 4:10-12፤ ፊልጵ. 4:13) በ2013 የዓመት መጽሐፍ (እንግሊዝኛ) ገጽ 101 አንቀጽ 3 እንዲሁም ከገጽ 111 አንቀጽ 3 እስከ ገጽ 112 አንቀጽ 2 ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። ምን ትምህርት እንዳገኙ አድማጮችን ጠይቅ።
10 ደቂቃ፦ “የማንን ትኩረት ሊስቡ ይችላሉ?” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። ትኩረታቸውን ሊስቡ የሚችሉ ርዕሰ ጉዳዮችን የያዙ መጽሔቶችን ልንሰጣቸው የምንችል በክልላችን የሚገኙ የንግድ ወይም ሌሎች ድርጅቶችን እንዲጠቅሱ አድማጮችን ጋብዝ።
መዝሙር 47 እና ጸሎት