ሰኔ 24 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ሰኔ 24 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 42 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
cf ምዕ. 7 ከአን. 17-21 እና ሣጥን (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ የሐዋርያት ሥራ 8-10 (10 ደቂቃ)
የቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ክለሳ (20 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ “አንድ ርዕሰ ጉዳይ ብቻ በማንሳት ሁለቱንም መጽሔቶች አበርክቱ።” በንግግር የሚቀርብ። ከንግግሩ በኋላ በቅርብ ጊዜ ለደረሰን መጠበቂያ ግንብ የተዘጋጀውን የአቀራረብ ናሙና በመጠቀም በሐምሌ ወር የመጀመሪያ ቅዳሜ እንዴት ጥናት ማስጀመር እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ የምናከናውነው ሥራ ከንቱ አይደለም። (ዕብ. 6:10) በ2013 የዓመት መጽሐፍ (እንግሊዝኛ) ከገጽ 113-115 ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። ምን ትምህርት እንዳገኙ አድማጮችን ጠይቅ።
10 ደቂቃ፦ በሐምሌና በነሐሴ የምናበረክተው ጽሑፍ። በውይይት የሚቀርብ። የብሮሹሮቹን አንዳንድ ገጽታዎች በአጭሩ ተናገር። ከብሮሹሮቹ መካከል ሁለቱን እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳዩ ሠርቶ ማሳያዎች እንዲቀርቡ አድርግ። አንደኛው ሠርቶ ማሳያ በገጽ 4 ላይ የሚገኘውን አቀራረብ ወይም በመጋቢት 2013 የመንግሥት አገልግሎታችን ላይ ከወጡት አቀራረቦች አንዱን በመጠቀም ምሥራች የተባለው ብሮሹር ሲበረከት የሚያሳይ መሆን ይኖርበታል።
መዝሙር 54 እና ጸሎት