ኅዳር 25 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ኅዳር 25 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 31 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
cf ምዕ. 15 ከአን. 1-7 (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ያዕቆብ 1-5 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ያዕቆብ 1:22 እስከ 2:13 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ፍቅር ፍርሃትን የሚያሸንፈው እንዴት ነው?—1 ዮሐ. 4:16-18 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ መጽሐፍ ቅዱስን በግል ማንበብ ብቻ በቂ ያልሆነው ለምንድን ነው?—rs ገጽ 327 አን. 2-3 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ በታኅሣሥ ወር መጽሔቶችን ለማበርከት የሚረዱ ሐሳቦች። በውይይት የሚቀርብ። መጽሔቶቹ በክልላችሁ ውስጥ ያሉ ሰዎችን ትኩረት ሊስቡ የሚችሉበትን ምክንያት ከ30 እስከ 60 ሴኮንድ ባለው ጊዜ ውስጥ ተናገር። ከዚያም በመጠበቂያ ግንብ መጽሔት የሽፋን ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ የሰዎችን የማወቅ ፍላጎት ለመቀስቀስ ምን ጥያቄ ማንሳት እንዳሰቡ አድማጮችን ጠይቅ፤ በመቀጠልም የትኞቹን ጥቅሶች ማንበብ እንዳሰቡ ጠይቅ። በንቁ! መጽሔት የሽፋን ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያም በተመሳሳይ መንገድ ጥያቄዎችን አቅርብ፤ ጊዜ ካለህ ከመጠበቂያ ግንብ ወይም ከንቁ! መጽሔት አንድ ተጨማሪ ርዕስ ማከል ትችላለህ። እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ ምን መልስ መስጠት ይኖርባችኋል? በአገልግሎት ትምህርት ቤት መጽሐፍ ገጽ 69 ከአንቀጽ 1-5 ላይ ተመሥርቶ የሚቀርብ ንግግር። አንድ አስፋፊ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቱ ራሱ ሊወስነው የሚገባውን ጉዳይ እሱ እንዲመልስለት በሚጠይቀው ጊዜ እንዴት መልስ እንደሚሰጥ የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ። ጥናቱ አስፋፊውን “አንተ በእኔ ቦታ ብትሆን ኖሮ ምን ታደርግ ነበር?” ብሎ ይጠይቀዋል።
10 ደቂቃ፦ “ለአገልግሎታችን የሚጠቅም ዓምድ።” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። “መጽሐፍ ቅዱሳዊ ውይይት” በሚለው ዓምድ ሥር በቅርቡ ከወጣ አንድ ርዕስ ላይ የተወሰነውን ክፍል በመጠቀም በአንቀጽ 3 ላይ የቀረበውን ዘዴ እንዴት ተግባራዊ ማድረግ እንደሚቻል የሚያሳይ አጭር ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
መዝሙር 45 እና ጸሎት