ጥር 6 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ጥር 6, 2014 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 46 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
cf ምዕ. 17 ከአን. 1-9 (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ዘፍጥረት 1-5 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ዘፍጥረት 4:1-16 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ የትክክለኛው ሃይማኖት አባሎች ስለ አምላክ መንግሥት በትጋት ይመሠክራሉ—rs ገጽ 328 አን. 5 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ አሮን—ለክርስቲያኖች ጥሩ ምሳሌ የሚሆንባቸው መንገዶች—w96 1/15 ገጽ 24-25 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ በጥር ወር መጽሔቶችን ለማበርከት የሚረዱ ሐሳቦች። በውይይት የሚቀርብ። መጽሔቶቹ በክልላችሁ ውስጥ ያሉ ሰዎችን ትኩረት ሊስቡ የሚችሉት እንዴት እንደሆነ ከ30 እስከ 60 ሴኮንድ ባለው ጊዜ ውስጥ ተናገር። ከዚያም በመጠበቂያ ግንብ መጽሔት የሽፋን ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ የሰዎችን የማወቅ ፍላጎት ለመቀስቀስ ምን ጥያቄ ማንሳት እንዳሰቡ አድማጮችን ጠይቅ፤ በመቀጠልም የትኞቹን ጥቅሶች ማንበብ እንዳሰቡ ጠይቅ። በንቁ! መጽሔት የሽፋን ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያም በተመሳሳይ መንገድ ጥያቄዎችን አቅርብ፤ ጊዜ ካለህ ከመጠበቂያ ግንብ ወይም ከንቁ! መጽሔት አንድ ተጨማሪ ርዕስ ማከል ትችላለህ። እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ ለጉባኤው እንደሚያስፈልግ ተጠቀሙበት።
10 ደቂቃ፦ ምን ትምህርት እናገኛለን? በውይይት የሚቀርብ። አንደኛ ቆሮንቶስ 9:19-23 እንዲነበብ አድርግ። ከዚያም ይህ ጥቅስ ከአገልግሎታችን ጋር በተያያዘ ሊጠቅመን የሚችለው እንዴት እንደሆነ ተወያዩበት።
መዝሙር 7 እና ጸሎት