ጥቅምት 13 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ጥቅምት 13 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 8 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 8 ከአን. 17-24 እና በገጽ 67 ላይ የሚገኝ ሣጥን (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ዘዳግም 4-6 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ዘዳግም 4:29-43 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ አምላክን ለማስደሰት መደረግ ያለባቸው ለውጦች—rs ገጽ 368 አን. 1-3 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ግብረ ሰዶም ምን ይናገራል?—rs ገጽ 367 አን. 3-5 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
5 ደቂቃ፦ በጥድፊያ ስሜት መስበክ ሲባል ምን ማለት ነው? በ2 ጢሞቴዎስ 4:2 ላይ ተመሥርቶ በግለት የሚቀርብ ንግግር። በመጋቢት 15, 2012 መጠበቂያ ግንብ ገጽ 16-17 ከአንቀጽ 7-9 ላይ የሚገኘውን ሐሳብ ተጠቀም።
10 ደቂቃ፦ የስብከቱ ሥራችን አጣዳፊ የሆነው ለምንድን ነው? በመጋቢት 15, 2012 መጠበቂያ ግንብ ገጽ 15-16 ከአንቀጽ 3-6 እና ገጽ 17-18 ከአንቀጽ 14-18 ላይ ተመሥርቶ በሽማግሌ የሚቀርብ ንግግር። በመንግሥት አገልግሎታችን ላይ “በአገልግሎት ረገድ ክህሎታችንን ማዳበር” በሚል አምድ ሥር በወጡት ተከታታይ ርዕሶች ውስጥ የሚገኙትን ሐሳቦች ተግባራዊ ማድረጋችን በጥድፊያ ስሜት እንድንሰብክ የሚረዳን እንዴት እንደሆነ ጎላ አድርገህ ግለጽ።
15 ደቂቃ፦ “የመንግሥቱን መልእክት ለማዳረስ ባገኛችሁት አጋጣሚ ሁሉ ተጠቀሙ!” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። አንቀጽ 3 ላይ ስትወያዩ መደበኛ ባልሆነ መንገድ በመመሥከር ያገኟቸውን ተሞክሮዎች እንዲናገሩ አድማጮችን ጋብዝ። የወሩን ጭብጥ ከክፍሉ ጋር በማዛመድ ክፍሉን ደምድም። በሚቀጥለው ሳምንት የአገልግሎት ስብሰባ ላይ “መጽሐፍ ቅዱሳዊ ውይይት” በሚለው ዓምድ ሥር በወጡ ሁለት ርዕሶች ላይ ስለምንወያይ አድማጮች ርዕሶቹን አንብበው እንዲመጡ አበረታታ።
መዝሙር 17 እና ጸሎት