ኅዳር 3 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ኅዳር 3 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 50 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 9 ከአን. 19-24 እና በገጽ 73 ላይ የሚገኝ ሣጥን (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ዘዳግም 14-18 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ዘዳግም 15:16 እስከ 16:8 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ኃጢአት የሚባል ነገር መኖሩን የምንቀበለው ለምንድን ነው?—rs ገጽ 371 አን. 3 እስከ ገጽ 372 አን. 3 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ጉዲፈቻ—የማደጎ ልጅ መሆን የሚያስከትለውን ስሜት መቋቋም—g 5/03 ገጽ 23-25፤ g 6/03 ገጽ 26-28 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ ልጆች ለአገልግሎት እንዲዘጋጁ መርዳት። በውይይት የሚቀርብ። የይሖዋ ወዳጅ ሁን—አገልግሎት እንውጣ የተባለውን ቪዲዮ አጫውት ወይም ይዘቱን በአጭሩ ከልስ። (jw.org/am ላይ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶች > ልጆች በሚለው ሥር ይገኛል) የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለልጆች አቅርብ፦ ከእናንተ መካከል የአገልግሎት ቦርሳ ያለው ማን ነው? በቦርሳችሁ ውስጥ ምን ነገሮችን ትይዛላችሁ? ሶፊያ መጀመሪያ ቦርሳዋ ውስጥ የከተተችው ምንድን ነው? ሌላስ ምን መያዝ ነበረባት? ሶፊያ ቦርሳዋን ካዘጋጀች በኋላ ከእናቷ ጋር ለማድረግ ያሰቡት አንድ በጣም አስፈላጊ ነገር አለ፤ ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? አንድ ልጅ (ሴትም ልትሆን ትችላለች) መጽሔት ሲያበረክት የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ አንዳንዶች ምሥራቹን በጥድፊያ ስሜት እየሰበኩ ያሉት እንዴት ነው? አንድ ሽማግሌ የአገልግሎት እንቅስቃሴያቸውን ለማስፋት ወይም አቅኚ ለመሆን ሲሉ አንዳንድ እርምጃዎችን ለወሰዱ ሁለት ወይም ሦስት አስፋፊዎች ቃለ መጠይቅ ያደርጋል። ጉባኤው ለመስክ አገልግሎት ያደረገውን ዝግጅት በመግለጽና ሁሉም በአገልግሎት የተሟላ ተሳትፎ ለማድረግ የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንዲወስዱ በማበረታታት ክፍሉን ደምድም።
10 ደቂቃ፦ ከአገልግሎት ጋር በተያያዘ ምን ማሻሻያዎች አድርጋችኋል? የአገልግሎት የበላይ ተመልካቹ በውይይት የሚያቀርበው። በቅርቡ “በአገልግሎት ረገድ ክህሎታችንን ማዳበር” በሚለው አምድ ሥር የወጡት ርዕሶች በአገልግሎት ረገድ በተለያዩ አቅጣጫዎች ማሻሻያ እንዲያደርጉ የረዷቸው እንዴት እንደሆነ ሐሳብ እንዲሰጡ አድማጮችን ጋብዝ። አስፋፊዎች በእነዚህ ርዕሶች ውስጥ የተሰጡትን ሐሳቦች ተግባራዊ በማድረግ በጥድፊያ ስሜት እንዲሰብኩ በማበረታታት ክፍሉን ደምድም።
መዝሙር 17 እና ጸሎት