ታኅሣሥ 8 የሚጀምር ሳምንት
ታኅሣሥ 8 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 6 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 11 ከአን. 13-19 (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ኢያሱ 1-5 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ኢያሱ 1:1-18 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ መንፈስ ቅዱስ ምንድን ነው?—rs ገጽ 379 አን. 1-3 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ምንዝር—አንድ ሰው በመንፈሳዊ ምንዝር የሚጠየቀው መቼ ነው?—w05 11/15 ገጽ 17-19 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
የወሩ ጭብጥ፦ ከተቀበልነው መልካም ነገር “ጥሩ ነገር” እናውጣ።—ማቴ. 12:35ሀ
10 ደቂቃ፦ በዚህ ወር የተዘጋጀልን “ጥሩ ነገር።” በንግግር የሚቀርብ። የወሩን ጭብጥ ግለጽ። (ማቴ. 12:35ሀ) እውነትን ካስተማረን ሰው መንፈሳዊ ሀብት ተቀብለናል። (የሚያዝያ 1, 2002 መጠበቂያ ግንብ ገጽ 16 ከአን. 5-7 ተመልከት።) እኛም በተራችን ያገኘነውን “ጥሩ ነገር” ለሌሎች ማካፈል አለብን። (ገላ. 6:6) በዚህ ወር ውስጥ በቀጣዮቹ ሳምንታት በአገልግሎት ስብሰባ ላይ የምናገኘውን “ጥሩ ነገር” በጉጉት እንዲጠብቁ አድርግ። የማስተማር ችሎታችንን ማሳደግ እንዲሁም አዳዲስ መዝሙሮችን መለማመድ ስለምንችልበት መንገድ እንማራለን።
20 ደቂቃ፦ “በአገልግሎት ረገድ ክህሎታችንን ማዳበር—የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት በተባለው መጽሐፍ እንዴት መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት እንደሚቻል ማሳየት።” በውይይት የሚቀርብ። ብቃት ያለው አስፋፊ ወይም አቅኚ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት በተባለው መጽሐፍ ተጠቅሞ እንዴት መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት እንደሚቻል ሲያሳይ በሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
መዝሙር 44 እና ጸሎት