ታኅሣሥ 15 የሚጀምር ሳምንት
ታኅሣሥ 15 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 1 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 12 ከአን. 1-8 እና በገጽ 96 ላይ የሚገኝ ሣጥን (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ኢያሱ 6-8 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ኢያሱ 8:18-29 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስ ያለው መሆኑ የሚረጋገጠው በምንድን ነው?—rs ገጽ 380 አን. 1-4 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ባላጋራ—ከሁሉ የከፋው ባላጋራችን ሰይጣን ዲያብሎስ ነው—w10 12/1 5-6 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
የወሩ ጭብጥ፦ ከተቀበልነው መልካም ነገር “ጥሩ ነገር” እናውጣ።—ማቴ. 12:35ሀ
15 ደቂቃ፦ “የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶችን ውጤታማ በሆነ መንገድ መምራት።” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። በአንቀጽ 3 ላይ ከተወያያችሁ በኋላ አንድ አስፋፊ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቱ ጋር የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት በተባለው መጽሐፍ ምዕራፍ 8 አንቀጽ 15 ላይ ሲወያይ የሚያሳይ ሁለት ክፍሎች ያሉት ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ። በመጀመሪያው ክፍል ላይ አስፋፊው ብዙ ይናገራል። በሁለተኛው ክፍል ላይ ደግሞ አስፋፊው፣ የአመለካከት ጥያቄዎች በመጠየቅ የጥናቱን አስተሳሰብ ለማስተዋል ጥረት ያደርጋል።
15 ደቂቃ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለመምራት ስንዘጋጅ የሚረዳን መሣሪያ። በውይይት የሚቀርብ። አድማጮች jw.org/am ላይ በሚገኘው “የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው?” በተባለው ክፍል ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ጋብዝ። (የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶች > ወጣቶች በሚለው ሥር ይገኛል) በዚህ ክፍል ውስጥ የሚገኙት ርዕሶች ወጣቶችንም ሆነ ትላልቅ ሰዎችን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማስጠናት የሚረዱን እንዴት እንደሆነ ተወያዩ። በእነዚህ ትምህርቶች ላይ የሚገኙት ጥያቄዎች የጥናቶቻችንን ልብ ለመንካት የሚያስችሉን እንዴት ነው? አንድ አስፋፊ ከእነዚህ ትምህርቶች አንዱን ተጠቅሞ፣ ስለ ጥናቱ ፍላጎት ሲያስብና ውጤታማ የሆኑ ጥያቄዎችን ሲዘጋጅ የሚያሳይ መነባንብ እንዲቀርብ አድርግ። አድማጮች ያሉንን ጥሩ ነገሮች ተጠቅመው የጥናቶቻቸውን ልብ ለመንካት ጥረት በማድረግ ረገድ የተሻሉ አስተማሪዎች እንዲሆኑ በማበረታታት ክፍሉን ደምድም።
መዝሙር 30 እና ጸሎት