መጋቢት 9 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
መጋቢት 9 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 44 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 15 ከአን. 13-20 (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ 1 ሳሙኤል 1-4 (8 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ 1 ሳሙኤል 2:30-36 (3 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መሲሑ ምን ትንቢት ተናግሯል?—nwt ገጽ 14 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ አሳ—ጭብጥ፦ ለንጹሑ አምልኮ ቅንዓት ይኑራችሁ—w14 8/15 ገጽ 17 አን. 4-6 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
የወሩ ጭብጥ፦ ‘ለመልካም ሥራ ሁሉ ዝግጁ ሁኑ።’—ቲቶ 3:1
10 ደቂቃ፦ “ለመልካም ሥራ ሁሉ ዝግጁ ሁኑ።” በወሩ ጭብጥ ላይ ተመሥርቶ የሚቀርብ ንግግር። ምሳሌ 21:5ን፣ ቲቶ 3:1ን እንዲሁም 1 ጴጥሮስ 3:15ን አንብብና አብራራ። ክርስቲያኖች ጥሩ ዝግጅት ማድረጋቸው ጠቃሚ የሆነው እንዴት እንደሆነ አብራራ። በዚህ ወር በአገልግሎት ስብሰባ ላይ የሚቀርቡትን አንዳንድ ክፍሎች በአጭሩ ከልስ፤ እንዲሁም ከወሩ ጭብጥ ጋር ያላቸውን ተያያዥነት ግለጽ።
10 ደቂቃ፦ ለቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት የበላይ ተመልካቹ ቃለ ምልልስ ማድረግ። በጉባኤው ውስጥ ምን ኃላፊነቶችን ትወጣለህ? በየሳምንቱ ትምህርት ቤቱን ለመምራት የምትዘጋጀው እንዴት ነው? ተማሪዎች የተሰጣቸውን ክፍል በሚገባ መዘጋጀት ያለባቸው ለምንድን ነው? አድማጮች ወደ ስብሰባ ከመምጣታቸው በፊት ክፍሎቹን ማንበባቸው ምን ጥቅሞች ያስገኝላቸዋል?
10 ደቂቃ፦ “ለመታሰቢያው በዓል እየተዘጋጃችሁ ነው?” በውይይት የሚቀርብ። መጋቢት 2013 የመንግሥት አገልግሎታችን ገጽ 2 ላይ የሚገኘውን ሐሳብ በአጭሩ ከልስ። አንድ አስፋፊ በመታሰቢያው በዓል ላይ የተገኘን እንግዳ ሞቅ ባለ ስሜት አቀባበል ሲያደርግለት የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
መዝሙር 8 እና ጸሎት