ከሰኔ 17-23
መዝሙር 51–53
መዝሙር 89 እና ጸሎት | የመግቢያ ሐሳብ (1 ደቂቃ)
1. ከባድ ስህተት እንዳንሠራ ምን ይረዳናል?
(10 ደቂቃ)
ከልክ በላይ በራሳችሁ አትተማመኑ፤ ሁሉም ሰዎች መጥፎ ነገር የማድረግ ዝንባሌ አላቸው (መዝ 51:5፤ 2ቆሮ 11:3)
ጥሩ መንፈሳዊ ልማድ ይኑራችሁ (መዝ 51:6፤ w19.01 15 አን. 4-5)
ንጹሕ ያልሆኑ ሐሳቦችንና ምኞቶችን ተዋጉ (መዝ 51:10-12፤ w15 6/15 14 አን. 5-6)
2. መንፈሳዊ ዕንቁዎች
(10 ደቂቃ)
3. የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ
(4 ደቂቃ) መዝ 51:1-19 (th ጥናት 12)
4. ውይይት መጀመር
(2 ደቂቃ) የአደባባይ ምሥክርነት። (lmd ምዕራፍ 7 ነጥብ 3)
5. ውይይት መጀመር
(2 ደቂቃ) ከቤት ወደ ቤት። (lmd ምዕራፍ 4 ነጥብ 4)
6. ተመላልሶ መጠየቅ
(3 ደቂቃ) መደበኛ ያልሆነ ምሥክርነት። ለግለሰቡ የአምላክን ስም አስተምረው። (lmd ምዕራፍ 9 ነጥብ 5)
7. ደቀ መዛሙርት ማድረግ
መዝሙር 115
8. ስህተታችሁን ለማረም እርምጃ ውሰዱ
(15 ደቂቃ) ውይይት።
ምንም ያህል ጥረት ብናደርግ ሁላችንም ስህተት መሥራታችን አይቀርም። (1ዮሐ 1:8) ስህተት በምንሠራበት ጊዜ፣ በኀፍረት ወይም ቅጣትን በመፍራት የይሖዋን ይቅርታና እርዳታ ከመፈለግ ወደኋላ ማለት የለብንም። (1ዮሐ 1:9) ምንጊዜም ቢሆን፣ ስህተታችንን ማረም የምንችልበት የመጀመሪያው እርምጃ የይሖዋን እርዳታ መጠየቅ ነው።
መዝሙር 51:1, 2, 17ን አንብብ። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦
ዳዊት የተናገራቸው ቃላት ከባድ ስህተት በምንሠራበት ጊዜ የይሖዋን እርዳታ እንድንጠይቅ የሚያነሳሱን እንዴት ነው?
የወጣትነት ሕይወቴ—ስህተቶቼን ማረም የምችለው እንዴት ነው? የተባለውን ቪዲዮ አጫውት። ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ጠይቅ፦
ተሊላን እና ጆዜን ስህተት ወደመሥራት የመሯቸው አንዳንድ ነገሮች የትኞቹ ናቸው?
ስህተታቸውን ለማረም የትኞቹን እርምጃዎች ወሰዱ?
እንዲህ ማድረጋቸው የጠቀማቸው እንዴት ነው?
9. የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
(30 ደቂቃ) bt ምዕ. 11 አን. 5-10፣ በገጽ 89 ላይ ያለው ሣጥን