የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 12/06 ገጽ 6
  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2006
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • መንፈሳዊነታችንን እንድንጠብቅ የሚረዳን የወረዳ ስብሰባ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2009
  • አዲስ የልዩ ስብሰባ ቀን ፕሮግራም
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2006
  • ‘በተገቢው ጊዜ የቀረበ ምግብ’
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2010
  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1996
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2006
km 12/06 ገጽ 6

አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም

ይህ ዓለም አሁን ያለንበት ሁኔታ ለዘላለም ይቀጥላል ብለን እንድናምን ይፈልጋል። የአምላክ ቃል ግን ከዚህ የተለየ ሐሳብ ይነግረናል። (1 ዮሐ. 2:15-17) ከዚህም ባሻገር በምድር ላይ ሀብት ማከማቸት ከንቱ ልፋት መሆኑን እንድንገነዘብ ይረዳናል። የ2007 የአገልግሎት ዓመት የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም “በሰማይ . . . ሀብት አከማቹ” የሚል ጭብጥ ያለው ሲሆን የአምላክ ሕዝቦች ያላቸውን አቋም ይበልጥ ያጠነክርላቸዋል።—ማቴ. 6:20

የመጀመሪያው ቀን:- በዚህ በችግር በተሞላ ዓለም ውስጥ የአምላክን መንግሥት ማስቀደም በእርግጥ ጠቃሚ ነው? የመጀመሪያው ተከታታይ ንግግር የተለያዩ ችግሮች ቢኖሩብንም እንኳ እንዲህ እንድናደርግ ያበረታታናል። ቀጣዮቹ ሁለት ንግግሮች ደግሞ መንፈሳዊ ሀብት ያለውን ከፍተኛ ዋጋ የሚያጎሉ ከመሆናቸውም ሌላ አገልግሎታችንን ለመፈጸም በይሖዋ ላይ መታመናችን አስፈላጊ መሆኑን ያብራራሉ።

ሁለተኛው ቀን:- ጊዜያችንን፣ ጉልበታችንንና ቁሳዊ ሀብታችንን በምን መንገድ ልንጠቀምበት እንመርጣለን? ሁለተኛው ተከታታይ ንግግር እነዚህን ነገሮች በጥበብ ልንጠቀምባቸው የምንችለው እንዴት እንደሆነ ያብራራል። የሕዝብ ንግግሩ አሁን ልንወስደው የሚገባንን እርምጃ ጎላ አድርጎ ይገልጻል። የመደምደሚያ ንግግሮቹ ደግሞ ቅድሚያ በምንሰጣቸው ነገሮች ረገድ ማስተካከያ ማድረግ ይገባን እንደሆነና እንዳልሆነ ለማወቅ ይረዱናል።

በመንፈሳዊ ገንቢ በሆነው በዚህ የሁለት ቀን ፕሮግራም ላይ ከተገኘን ‘በሰማይ ለራሳችን ሀብት እንድናከማች’ የሚያበረታታ ትምህርት እናገኛለን!

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ