የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • wp22 ቁጥር 1 ገጽ 4-5
  • ጥላቻ የተስፋፋው ለምንድን ነው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ጥላቻ የተስፋፋው ለምንድን ነው?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2022
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ጥላቻ ምንድን ነው?
  • ጥላቻ የሚጀመረው እንዴት ነው?
  • የሚስፋፋው እንዴት ነው?
  • መጽሐፍ ቅዱስ የጥላቻን ምንጭ ይነግረናል
  • ጥላቻን ድል ማድረግ እንችላለን!
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2022
  • ጥላቻ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይወገዳል!
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2022
  • ጥላቻ ይህን ያህል የበዛው ለምንድን ነው?
    ንቁ!—1998
  • ጥላቻ ይህን ያህል የበዛው ለምንድን ነው?—መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2022
wp22 ቁጥር 1 ገጽ 4-5

ጥላቻ የተስፋፋው ለምንድን ነው?

ዓለማችን ይህን ያህል በጥላቻ የተሞላው ለምንድን ነው? ምክንያቱን ለማወቅ የጥላቻን ምንነት፣ ጥላቻ የሚጀመረው እንዴት እንደሆነ እንዲሁም እንዴት እንደሚስፋፋ ማወቅ ይኖርብናል።

ጥላቻ ምንድን ነው?

ጥላቻ አንድን ሰው ወይም አንድን ቡድን የመጸየፍ ወይም ፀር የመሆን ስሜት ነው። ጥላቻ ለአጭር ጊዜ ከሚቆይ የብስጭት ስሜት የዘለለ ነው።

ጥላቻ የሚጀመረው እንዴት ነው?

ሰዎች ሌሎችን መጥላት እንዲጀምሩ የሚያደርጓቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ። ብዙዎች የጥላቻ ሰለባ የሚሆኑት ባደረጉት ነገር የተነሳ ሳይሆን በማንነታቸው የተነሳ ነው። እነዚህ ሰዎች ክፉ እንደሆኑ፣ ሌሎችን እንደሚጎዱ ወይም መሻሻል እንደማይችሉ ተደርገው ሊቆጠሩ ይችላሉ። ዝቅተኛ እንደሆኑ፣ አደጋ እንደሚያደርሱ ወይም ችግር ፈጣሪ እንደሆኑ ተደርገው ሊታዩም ይችላሉ። ብዙዎች ለሌሎች ጥላቻ የሚያድርባቸው ቀደም ሲል በደረሰባቸው ዓመፅ፣ የፍትሕ መጓደል ወይም ሌላ መጥፎ ነገር የተነሳ ሊሆን ይችላል።

የሚስፋፋው እንዴት ነው?

አንድ ሰው ጨርሶ አግኝቶ የማያውቀውን ሰው እንኳ ሊጠላ ይችላል። ለምሳሌ ያህል፣ አንድ ሰው የሚወዳቸውና የሚቀርባቸው ሰዎች ያላቸውን የተዛባ አመለካከት ሳያስበው ሊወርስ ይችላል። በዚህ መንገድ ጥላቻ በቀላሉ ይዛመታል፤ ብዙም ሳይቆይ መላው ማኅበረሰብ ተመሳሳይ አመለካከት ሊያዳብር ይችላል።

ጥላቻ ያለውን የመዛመት ኃይል ስንረዳ ይህን ያህል የተስፋፋው ለምን እንደሆነ ግልጽ ይሆንልናል። ይሁንና ዓለምን ተብትቦ የያዘውን የጥላቻ ሰንሰለት ለመበጠስ የጥላቻን አነሳስ ማወቅ ይኖርብናል። መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ ጉዳይ ይነግረናል።

መጽሐፍ ቅዱስ የጥላቻን ምንጭ ይነግረናል

አንዳቸው ወደ ሌላው የሚያመሩ ሁለት ቀስቶች፤ የጥላቻን ሰንሰለት ወይም ዑደት የሚያመለክቱ ናቸው። 1. የተዛባ መረጃ፤ የሌሎች ተጽዕኖን፣ ማኅበራዊ ሚዲያን እና የዜና ማሰራጫዎችን ያካትታል። 2. ስለ ባሕል፣ ስለ ዘር ወይም ስለ ሃይማኖት አለማወቅ። 3. ለውጥን፣ ማጣትን ወይም ነገን መፍራት። 4. ጥላቻ፤ አድልዎን፣ ማግለልንና ዓመፅን ያካትታል።

ጥላቻ የጀመረው ከሰዎች አይደለም። ጥላቻ የጀመረው አንድ የሰማይ መልአክ በአምላክ ላይ ባመፀበት ጊዜ ነው፤ ይህ መልአክ ከጊዜ በኋላ ሰይጣን ዲያብሎስ ተብሎ ተጠርቷል። ዲያብሎስ ዓመፁን “ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ነፍሰ ገዳይ ነበር።” “ውሸታምና የውሸት አባት” ስለሆነ ጥላቻንና ዓመፅን ማነሳሳቱን ቀጥሏል። (ዮሐንስ 8:44፤ 1 ዮሐንስ 3:11, 12) መጽሐፍ ቅዱስ፣ ዲያብሎስ ክፉ፣ ብስጩና ቁጡ እንደሆነ ይገልጻል።—ኢዮብ 2:7፤ ራእይ 12:9, 12, 17

ፍጹም ያልሆኑ ሰዎች የጥላቻ ዝንባሌ አላቸው። የመጀመሪያው ሰው አዳም የሰይጣንን የኃጢአት ጎዳና ተከትሏል። በመሆኑም የሰው ልጆች በሙሉ ኃጢአትንና አለፍጽምናን ወርሰዋል። (ሮም 5:12) የአዳም የበኩር ልጅ የሆነው ቃየን በጥላቻ ተነሳስቶ የገዛ ወንድሙን አቤልን ገድሎታል። (1 ዮሐንስ 3:12) እርግጥ ነው፣ ፍቅርና ርኅራኄ የሚያሳዩ ብዙ ሰዎች አሉ። ሆኖም ኃጢአትን ስለወረስን ብዙዎች ለጥላቻ መንስኤ የሆኑትን እንደ ራስ ወዳድነት፣ ምቀኝነትና ኩራት ያሉትን ባሕርያት ያንጸባርቃሉ።—2 ጢሞቴዎስ 3:1-5

አለመቻቻል ጥላቻን ያቀጣጥላል። የምንኖርበት ዓለም ጭካኔንና ጎጂ ባሕርያትን በማስፋፋት ጥላቻን ያባብሳል። ‘መላው ዓለም በክፉው ማለትም በሰይጣን ዲያብሎስ ቁጥጥር ሥር ስለሆነ’ አለመቻቻል፣ መድልዎ፣ ስድብ፣ ጉልበተኝነትና ሥርዓት አልበኝነት ተስፋፍቷል።—1 ዮሐንስ 5:19

ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ የጥላቻን መንስኤ በመናገር ብቻ አያበቃም። መፍትሔውንም ይጠቁመናል።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ