የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • wp25 ቁጥር 1 ገጽ 3
  • የጦርነት ሰቆቃ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የጦርነት ሰቆቃ
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2025
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ወታደሮች
  • ንጹሐን ዜጎች
  • ጦርነት እና ግጭት ቢኖርም ሰላም ማግኘት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2025
  • የዩክሬን ጦርነት ሁለተኛ ዓመቱን ያዘ—መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጠው ተስፋ አለ?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ጦርነት የሚያስከትለው ኪሳራ የገንዘብ ብቻ ነው?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ጦርነት እና ግጭት ሁላችንንም የሚነካን እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2025
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2025
wp25 ቁጥር 1 ገጽ 3
ሥዕሎች፦ 1. የአንድን ወታደር ግንባርና ዓይን የሚያሳይ የተቀደደ ፎቶግራፍ። 2. የአንዲትን አረጋዊት ሴት ግንባርና ዓይን የሚያሳይ የተቀደደ ፎቶግራፍ።

የጦርነት ሰቆቃ

የጦርነትንና የግጭትን ያህል በሰዎች ሕይወት ላይ የከፋ ተጽዕኖ የሚያሳድር ነገር የለም ማለት ይቻላል። በዓለም ዙሪያ የሚኖሩ ወታደሮችና ንጹሐን ዜጎች የጦርነትን ሰቆቃ በዓይናቸው ተመልክተዋል።

ወታደሮች

“በዙሪያችን ሰዎች ሲገደሉና ሲቆስሉ እናያለን። ቀን ከሌት በስጋት ነው የምንኖረው።”—ጌሪ፣ ብሪታንያ

“ጀርባዬና ፊቴ ላይ በጥይት ተመትቻለሁ፤ ልጆችንና አረጋውያንን ጨምሮ ብዙዎች ሲገደሉ አይቻለሁ። ጦርነት ልብ ያደነድናል።”—ዊልማር፣ ኮሎምቢያ

“ከፊት ለፊትህ አንድ ሰው ተተኩሶበት ሲገደል ስታይ ትዕይንቱ ከአእምሮህ አይጠፋም። ያሰማው ጩኸትና ሲቃ ያቃጭልብሃል። ግለሰቡን ፈጽሞ አትረሳውም።”—ዘፊራ፣ ዩናይትድ ስቴትስ

ንጹሐን ዜጎች

“መልሼ ደስተኛ መሆን የምችል አልመሰለኝም ነበር። ለሕይወትህ ትሰጋለህ፤ ከዚህም በላይ ደግሞ ለቤተሰቦችህና ለጓደኞችህ ሕይወት ትሰጋለህ።”—ኦሌክሳንድራ፣ ዩክሬን

“ከአሁን አሁን ተባራሪ ጥይት መታኝ ብለው እየተሳቀቁ ከሌሊቱ 8 ሰዓት እስከ ምሽቱ 5 ሰዓት ድረስ ለምግብ መሰለፍ በጣም ያስፈራል።”—ዴለር፣ ታጂኪስታን

“ጦርነት ወላጆቼን ነጥቆኛል። ብቻዬን ስለቀረሁ የሚያጽናናኝም ሆነ የሚንከባከበኝ ማንም ሰው አልነበረም።”—ማሪ፣ ሩዋንዳ

ከላይ የተጠቀሱት ሰዎች የጦርነትን ሰቆቃ ያዩ ቢሆንም ሰላም ማግኘት ችለዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ ማንኛውም ዓይነት ጦርነትና ግጭት በቅርቡ እንደሚያበቃ እርግጠኞች ናቸው። ይህ የሚሆነው እንዴት እንደሆነ ይህ መጠበቂያ ግንብ መጽሔት መጽሐፍ ቅዱስን ተጠቅሞ ያብራራል።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ