የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ቅዳሜ፣ ሐምሌ 26

የተወደዳችሁ ልጆቹ በመሆን አምላክን የምትመስሉ ሁኑ።—ኤፌ. 5:1

በዛሬው ጊዜ ቅንዓት፣ አመስጋኝነትና ፍቅር በሚንጸባረቅበት መንገድ ስለ ይሖዋ በመናገር እሱን ማስደሰት እንችላለን። አገልግሎት ስንወጣ ዋነኛው ዓላማችን ሰዎች ወደ ይሖዋ እንዲቀርቡ እንዲሁም ለሰማዩ አባታችን የእኛ ዓይነት አመለካከት እንዲያዳብሩ መርዳት እንደሆነ አንዘነጋም። (ያዕ. 4:8) ለሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ይሖዋ ምን እንደሚል ማለትም እንደ ፍቅር፣ ፍትሕ፣ ጥበብና ኃይል ያሉትን ባሕርያቱን እንዴት አድርጎ እንደሚገልጽ ስናሳያቸው ደስ ይለናል። በተጨማሪም ይሖዋን ለመምሰል የቻልነውን ሁሉ በማድረግ እሱን ማወደስና ማስደሰት እንችላለን። እንዲህ ስናደርግ በዚህ ክፉ ዓለም ውስጥ ካሉት ሰዎች የተለየን እንደሆንን ይታያል። (ማቴ. 5:14-16) ሰዎች የተለየን መሆናችንን ሲያስተውሉ ምክንያቱን ማወቅ ይፈልጉ ይሆናል። በዕለት ተዕለት ሕይወታችን ከሰዎች ጋር ስንገናኝ የተለየን የሆንበትን ምክንያት ልናብራራላቸው እንችላለን። በዚህም የተነሳ ቅን ልብ ያላቸው ሰዎች ወደ አምላካችን ለመቅረብ ይነሳሳሉ። በእነዚህ መንገዶች ይሖዋን ስናወድስ ልቡን እናስደስታለን።—1 ጢሞ. 2:3, 4፤ w24.02 10 አን. 7

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

እሁድ፣ ሐምሌ 27

ማበረታታትም ሆነ . . . መውቀስ [የሚችል] ሊሆን ይገባል።—ቲቶ 1:9

ጎልማሳ ክርስቲያን መሆን ከፈለጋችሁ ጠቃሚ ክህሎቶችን ማዳበር ይኖርባችኋል። እንዲህ ማድረጋችሁ በጉባኤ ውስጥ ኃላፊነት ለመቀበል፣ ራሳችሁን ወይም ቤተሰባችሁን ለማስተዳደር የሚያስችል ሥራ ለመያዝ እንዲሁም ከሌሎች ጋር ጥሩ ዝምድና ለመመሥረት ይረዳችኋል። ለምሳሌ ጥሩ የማንበብና የመጻፍ ችሎታ አዳብሩ። መጽሐፍ ቅዱስ ደስተኛና ስኬታማ የሆነ ሰው በየዕለቱ የአምላክን ቃል እንደሚያነብና እንደሚያሰላስልበት ይናገራል። (መዝ. 1:1-3) አንድ ሰው መጽሐፍ ቅዱስን በየዕለቱ ማንበቡ የይሖዋን አስተሳሰብ ለመረዳት ያስችለዋል፤ ይህ ደግሞ አጥርቶ ለማሰብና በሚገባ ለማመዛዘን ይረዳዋል። (ምሳሌ 1:3, 4) ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሠረተ መመሪያና ምክር ለማግኘት ብቃት ያላቸው ወንድሞች እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። ጥሩ የማንበብና የመጻፍ ችሎታ ካላችሁ ግንዛቤ የሚያሰፉና እምነት የሚያጠናክሩ ንግግሮችንና ሐሳቦችን መዘጋጀት ትችላላችሁ። በተጨማሪም ጥሩ ማስታወሻ በመያዝ እምነታችሁን ማጠናከር እንዲሁም ሌሎችን ማበረታታት ትችላላችሁ። w23.12 26-27 አን. 9-11

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ሰኞ፣ ሐምሌ 28

ከእናንተ ጎን ያለው፣ ከዓለም ጎን ካለው ይበልጣል።—1 ዮሐ. 4:4

ፍርሃት በሚሰማህ ጊዜ ይሖዋ ወደፊት ሰይጣን ሲጠፋ በሚያደርገው ነገር ላይ አሰላስል። በ2014 የክልል ስብሰባ ላይ የቀረበ አንድ ሠርቶ ማሳያ አንድ አባት 2 ጢሞቴዎስ 3:1-5 በገነት ውስጥ የሚኖረውን ሕይወት የሚገልጽ ቢሆን ኖሮ ምን ይል እንደነበር ከልጆቹ ጋር ሲወያይ አሳይቶን ነበር፦ “በአዲሱ ዓለም እጅግ አስደሳች የሆነ ዘመን እንደሚመጣ ይህን እወቅ። ምክንያቱም ሰዎች ሌሎችን የሚወዱ፣ መንፈሳዊ ሀብት የሚወዱ፣ ልካቸውን የሚያውቁ፣ ትሑቶች፣ አምላክን የሚያወድሱ፣ ለወላጆች የሚታዘዙ፣ የሚያመሰግኑ፣ ታማኝ የሆኑ፣ ለቤተሰባቸው ጥልቅ ፍቅር ያላቸው፣ ለመስማማት ፈቃደኞች የሆኑ፣ ሁልጊዜ ስለ ሌሎች መልካም ነገር የሚያወሩ፣ ራሳቸውን የሚገዙ፣ ገሮች፣ ጥሩ ነገር የሚወዱ፣ ታማኞች፣ እሺ ባዮች፣ ራሳቸውን ዝቅ የሚያደርጉ፣ ሥጋዊ ደስታን ከመውደድ ይልቅ አምላክን የሚወዱ ይሆናሉ፤ ከልብ ለአምላክ ያደሩ ናቸው፤ ከእነዚህ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ይኑርህ።” በአዲሱ ዓለም ስለሚኖረው ሕይወት ከቤተሰቦችህ ወይም ከእምነት ባልንጀሮችህ ጋር የመወያየት ልማድ አለህ? w24.01 6 አን. 13-14

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ