-
‘የአምላክ ጥበብ እንዴት ጥልቅ ነው!’መጠበቂያ ግንብ—2011 | ግንቦት 15
-
-
17. ይሖዋ የወሰደው እርምጃ “ከተፈጥሮ ውጭ በሆነ መንገድ” የተከናወነ ነው ሊባል የሚችለው እንዴት ነው?
17 ይሖዋ፣ ብዙዎች ፈጽሞ የማይመስል እንደሆነ የሚሰማቸውን ነገር አድርጓል። ጳውሎስ፣ ይሖዋ የወሰደው እርምጃ “ከተፈጥሮ ውጭ በሆነ መንገድ” የተከናወነ እንደሆነ ገልጿል። (ሮም 11:24) ይህ የሆነው እንዴት ነው? የዱር የወይራ ዛፍ ቅርንጫፍን በእርሻ ላይ በተተከለ የወይራ ዛፍ ላይ ማጣበቅ ያልተለመደ እንዲያውም ከተፈጥሮ ውጭ የሆነ ተግባር ይመስል ይሆናል፤ ሆኖም በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበሩ አንዳንድ ገበሬዎች እንዲህ ያደርጉ ነበር።b ከዚህ ጋር በሚመሳሰል መንገድ ይሖዋም በጣም አስገራሚ የሆነ ነገር አድርጓል። አይሁዳውያን፣ አሕዛብ በአምላክ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ፍሬ ማፍራት እንደማይችሉ ይሰማቸው ነበር። ይሁንና ይሖዋ፣ አሕዛብን የመንግሥት ፍሬ የሚያፈራ “ሕዝብ” ክፍል አደረጋቸው። (ማቴ. 21:43) ወደ ክርስትና የተለወጠ የመጀመሪያው ያልተገረዘ አሕዛብ የሆነው ቆርኔሌዎስ በ36 ዓ.ም. በመንፈስ ከተቀባበት ጊዜ ጀምሮ አይሁዳውያን ያልሆኑ ያልተገረዙ ሰዎች በምሳሌያዊው የወይራ ዛፍ ላይ የመጣበቅ አጋጣሚ ተከፈተላቸው።—ሥራ 10:44-48c
18. ሥጋዊ አይሁዳውያን ከ36 ዓ.ም. በኋላ ምን አጋጣሚ ነበራቸው?
18 እንዲህ ሲባል ሥጋዊ አይሁዳውያን ከ36 ዓ.ም. በኋላ የአብርሃም ዘር ክፍል ለመሆን ምንም አጋጣሚ አልነበራቸውም ማለት ነው? አይደለም። ጳውሎስ እንዲህ ብሏል፦ “እነሱም [ሥጋዊ አይሁዳውያን] ቢሆኑ እምነት የለሽ ሆነው በዚያው ካልቀጠሉ ተመልሰው ይጣበቃሉ፤ ምክንያቱም አምላክ ዳግመኛ ሊያጣብቃቸው ይችላል። አንተ በተፈጥሮ የዱር ከሆነው የወይራ ዛፍ ተቆርጠህ ከተፈጥሮ ውጭ በሆነ መንገድ በጓሮ የወይራ ዛፍ ላይ መጣበቅ ከቻልክ እነዚህ ተፈጥሯዊ የሆኑት ቅርንጫፎችማ በራሳቸው የወይራ ዛፍ ላይ መጣበቅ እንደሚችሉ የታወቀ ነው!”d—ሮም 11:23, 24
-