የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኤውንቄና ሎይድ በአርዓያነት የሚጠቀሱ አስተማሪዎች
    መጠበቂያ ግንብ—1998 | ግንቦት 15
    • ይሁን እንጂ ኤውንቄ የእምነት አጋር አላጣችም። ጢሞቴዎስ “ቅዱሳን መጻሕፍትን” የተማረው ከእናቱና በእናቱ በኩል አያቱ ከሆነችው ከሎይድ ነበር።a ሐዋርያው ጳውሎስ ጢሞቴዎስን እንዲህ ሲል አጥብቆ መክሮታል:- “አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት [“እንድታምን በተደረግህበት፣” NW] ነገር ጸንተህ ኑር፣ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፣ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል።”​—⁠2 ጢሞቴዎስ 3:​14, 15

  • ኤውንቄና ሎይድ በአርዓያነት የሚጠቀሱ አስተማሪዎች
    መጠበቂያ ግንብ—1998 | ግንቦት 15
    • ጢሞቴዎስ ቅዱስ ጽሑፋዊ እውነቶችን ‘እንዲያምን ተደርጎ’ ነበር። በአንድ የግሪክኛ መዝገበ ቃላት መሠረት ጳውሎስ እዚህ ላይ የተጠቀመበት ቃል አንድን ነገር “በጽኑ እንዲያምን ማድረግ፤ እርግጠኛ እንዲሆን ማድረግ” የሚል ትርጉም አለው። በጢሞቴዎስ ልብ ውስጥ እንዲህ ያለውን ጽኑ እምነት መትከልና ከአምላክ ቃል እያስረዱ በቃሉ ላይ እምነት እንዲኖረው ማድረግ ብዙ ጊዜና ከፍተኛ ጥረት የሚጠይቅ እንደነበር አያጠራጥርም። ኤውንቄና ሎይድ ጢሞቴዎስን ከቅዱሳን ጽሑፎች ለማስተማር በጋራ ጠንከረው መሥራታቸውን ከዚህ መገንዘብ ይቻላል። እነዚህ አምላካዊ ሴቶች ምንኛ ተክሰዋል! ጳውሎስ ስለ ጢሞቴዎስ ሲጽፍ “በአንተ ያለውን ግብዝነት የሌለበትን እምነትህን አስባለሁ፤ ይህም እምነት ቀድሞ በአያትህ በሎይድ በእናትህም በኤውንቄ ነበረባቸው፣ በአንተም ደግሞ እንዳለ ተረድቼአለሁ” ለማለት ችሎ ነበር።​—⁠2 ጢሞቴዎስ 1:​5

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ